Sunday, April 21, 2013

የሕወሓት/ኢሕአዴግ መንግሥት ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ዘመቻ እያካሄደ ነው




ከኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የጋራ እንቅስቃሴ አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ
Ethiopian flag, Green, yellow and red
ሚያዝያ 12 ቀን 2005 ዓ.ም. (April 20, 2013)
ኢትዮጵያ የብዙ ብሔረሰቦችና ሀይማኖት ተከታዮች ሀገር ናት። እነዚህ ብሔረሰቦች ለብዙ ዘመናት በአንድነትና በሕብረት ተደጋግፈው፤ ተጋብተውና ተስማምተው ኖረዋል። ከውጭ የመጣባቸውን ጠላትም በተባበረ ክንዳቸው መክተው በመመለስ በዓለም ታዋቂ ታረክ አስመዝግበዋል። በአሁኑ ወቅት ከመሀከላቸው የበቀሉ ተንኮለኞች  ለፓለቲካ ሥልጣንና ለግል ጥቅም ማራመጃ ሲሉ የሚያካሂዱትን የመከፋፈል እርምጃ የኢትዮጵያ ሕዝብ  በተከታታይ እያከሸፈው ቢሆንም፤ በአሁኑ ወቅት በጦር ኃይል እያስገደዱ በአንድ ብሔረስብ ላይ ያተኮረ  አስከፊና አደገኛ የዘር ማጥፋት ተግባር እያከናወኑ ይገኛሉ።
ይህንን ሰላም ወዳድና በሰላም የኖረ ሕዝብ እርስ በራሱ በማጋጨትና አንዱ በአንዱ ላይ እንዲነሳሳ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ ግንባር/ሕወሓት መሪዎች ከፅንሳቸው ጀምረው በፖሊሲ ደረጃ ነድፈው እስካሁን በማስፈጸም ላይ ይገኛሉ። ወደፊትም በሥልጣናቸው ለመቆየትና ከሕዝብ የሚዘርፉትን ንብረት ካለምንም ተቃውሞ ለማካሄድ ወገኖቻችንን በዘርና በቋንቋ በመለያየት ለዘመናት ከኖሩበት አካባቢ ጭካኔ በተመላበት ሁኔታ ሆን ተብሎ በተቀየስ የዘር ማጥራት ፖሊሲ አማካኝነት ለጊዜው ከተወሰኑ ክልሎች በማፈናቀል ላይ ናቸው።

Saturday, April 20, 2013


Ethiopia: Norway police stopped meeting

There was general consul at the Ethiopian Embassy, ​​Abay Mebrat Beyene, who would chair the meeting with embassy secretary. The main theme was collecting money in the Ethiopian exile to a very controversial prestige project for the regime in Ethiopia. Read more…

World Bank Must End its Support for Human Rights Abuses in Ethiopia


A multi-billion dollar aid program administered by the World Bank is underwriting systematic human rights abuses in

The Mursi tribe in Mago national park, Ethiopia, 2011.
The Mursi tribe in Mago national park, Ethiopia, 2011. Photograph: Patricia White/Alamy
Ethiopia. Last September, Ethiopian victims submitted a complaint about the program to the World Bank Inspection Panel, which is tasked with investigating whether or not the Bank complies with its own policies to prevent social and environmental harm.  A meeting of the Bank’s board of directors to discuss the Panel’s preliminary findings was postponed on March 19th due to objections from the Ethiopian government.
Ethiopia is one the largest aid recipients in the world, receiving approximately US$3 billion annually from external donors. The largest aid program, financed by the World Bank, the UK, the European Commission and other Western governments, is called Promotion of Basic Services (PBS).  It aims to expand access to services in five sectors: education, health, agriculture, water supply and sanitation, and rural roads. The PBS program objectives are indisputably laudable and aim to meet a number of dire needs of the Ethiopian population. There is evidence, however, that it is contributing to a government campaign to forcibly resettle an estimated 1.5 million people.

Protest rally in Oslo, Norway: Against the recent forceful eviction of Amharas


Protest rally in Oslo, Norway: Against the recent forceful eviction of Amharas

Ethiopians in Norway have held a great and spectacular demonstration
Ethiopians in Norway have held a great and spectacular demonstration opposing the recentevictions of ethnic Amharas from different parts of Ethiopia and demanding freedom in Ethiopia.
The demonstrators in their huge numbers showed their anger and frustration walking through the main street in Oslo and chanting slogans denouncing the barbaric act of the TPLF regime and demanding democracy and regime change in Ethiopia.
The participants in the demonstration were different organizations, political parties, supporting organs, civic organizations, religious groups and independent individuals reflecting Ethiopians unity and colorfulness!
The demonstrators have also meet the representative of the Norwegian parliament –Stortinget, and delivered their appeal.
In this demonstration Ethiopians in Norway not only showed their solidarity with all victims of TPLF in Ethiopia, but also confirmed their determination to confront any activities what so ever done in Norway by TPLF in the name of Ethiopian people!

ይህጉዳያችን ካልሆነ ምን ጉዳያችን ሊሆን ይችላል?


ይህጉዳያችን ካልሆነ ምን ጉዳያችን ሊሆን ይችላል?

ኢትዮጵያ መሬት ባከራየቻቸውም ሆነ ከሸጠችላቸው ኩባንያዎች ሃገራት ጋር ክርክር ቢነሳ ጉዳዩ የሚታየው በአለም አቀፍ ገላጋይ ፍርድቤት ነው


ኢጣልያ በሰሜናዊው የኢትዮጵያ ክፍል በኤርትራ ለመጀመርያ ጊዜ ቦታ ማግኘት የጀመረችው በ አሰብ ግዛት ሩባርቲኖ በተባለ የመርከብ ኩባንያ አማካይነት ከአንድ ሱልጣን በ1869 ዓም በገዛችው ትንሽ መሬት መሆኑ ይታወቃል። እንግዲህ ሃገራችንን ከ አንድ መቶ አመታት በላይ አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረስ የቀጠለ ፖለቲካዊም ሆነ ምጣኔ ሃብታዊ ችግር እየፈጠረ መሆኑ ይታወቃል።

ESAT Ethiopian News Amsterdam April 19, 2013

ESAT is the first independent Ethiopian Satellite Television service and Radio Station who broadcast to Ethiopia and the rest of the world. ESAT Ethiopian News Amsterdam April 19, 2013.

መልዕክተ ቹቸቤ ክፍል ሁለት ቁጥር አሥራ ሁለት (ECADF)


መልዕክተ ቹቸቤ ክፍል ሁለት ቁጥር አሥራ ሁለት (ECADF)

  • በቹቸቤ

በመላው አለም የተበታተኑ ግን በአላማ አንድ የሆኑ ኢትዮጵያያውያን በያሉበት ሁሉ ይተጋሉ። ከኒህ ኢትዮጵያውያን መካከልም የ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች መወያያ መድረክ ታዳሚዎች በየሀገራቱ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው። ያንን በተመለከተ ትንሽ ብለናል። የቅራኔ አፈታታችን ማሸነፍ ወይም መሸነፍ እየበዛበት በቀላሉ ሊፈቱ የሚችሉ ጉዳዮች እየከረሩ አጥፊና ጠፊ እያረጉን ነው። ይህ በፖለቲካም በማህበራዊም ሆነ ሀይማኖታዊ ተቋማት ሁሉ እየተንጸባረቀ ነው። በዚህ ጉዳይም ለውይይት መንደርደርያ ያህል ምሳሌዎች ቀርበዋል። የትግራይ ተገንጣይ ድርጅት መሪዎች አባሎችና ደጋፊዎቻቸው በስህተት ላይ ስህተት በጥፋት ላይ ጥፋት እያከሉበት በመጨረሻ የግራዚያኒ ትቆርቋሪ ሆነው ኢትዮጵያውያንን በጅምላ ማሰራቸው እጅግ አሳሳቢና አነጋጋሪ ጉዳይ እንደሆነ ተዘክሮአል ስነ ግጥም ቀርቦአል። የመሰብሰብ ነፃነትን የመወያየት ነፃነት የተሟጠጠበት ሀገር መሆኑንም በሰማያዊ ፓርቲ ላይ የደረሰውን በደል እንደምሳሌ አቅርበናል።

Monday, April 8, 2013

በዋሽንግቶን ዲሲ ኢትዮጵያውያን ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ


በዋሽንግቶን ዲሲ ኢትዮጵያውያን ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

ECADF – በአማራ ብሄር ተወላጆች ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ በመቃወም ከወትሮው እጅግ ቁጥሩ የበዛ ሰላማዊ ሰልፈኛ የተገኘበት ደማቅ የተቃውሞ ሰልፍ በሗይታውስ ፊት ለፊት ዛሬ ከጠዋቱ 9pm ጀምሮ ሲደረግ አርፍዷል።
ሰልፉን ያስተባበሩ ታዋቂ የመብት ተሟጋቾች እንዳሉት ከሆነ ይህ አይነቱ ተቃውሞ በሌሎች ሀገሮችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው።

Sunday, April 7, 2013

“አይቴ ብሔሩ ለአማራ . . . የአማራ አገሩ ወዴት ነው?” ኢትዮጵያ አይደለምን?


“አይቴ ብሔሩ ለአማራ . . . የአማራ አገሩ ወዴት ነው?” ኢትዮጵያ አይደለምን?
(ኤፍሬም እሸቴ – www.adebabay.com)፦ በንግግርም ይሁን በጽሑፍ ለማንሣትም ሆነ ለመጥቀስ፣ ለመወያየትም ሆነ ለመከራከር ከማይመቹኝ (discomfort እንዲል ፈረንጅ) የኢትዮጵያ ርዕሰ ጉዳዮች ሁሉ ዘርን፣ ብሔረሰብን የተመለከተው ዋነኛውና አንዱ ነው። ጉዳዩ በዕለት ተዕለት የአገራችን ሕይወት ውስጥ ወሳኙ እና በሁነኛ መልክ ማኅበረሰባዊ ማንነታችንን እየበየነ እንዳለ እያወቅኹም እንዲህ እንደ አሁኑ በአደባባይ ለመውጣት ግን ብዙም አይቀለኝም። ምክንያቱ ሌላ ምንም ሳይሆን ጉዳዩ ያለው ስሱነት (sensitivity) ነው። አሁን ግን ላልፈው አልቻልኩም። አይገባምም። ለምን?

ማፈናቀሉ እስከመቼ?


ማፈናቀሉ እስከመቼ?

ብስራት ወልደሚካኤል
ህወሓት/ኢህአዴግ በህይወቱ ከሚፈራውና ከሚጠላው ነገር አንዱ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ ማየትና መስማት ነው፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ አባላት በባህሪያቸው በውሸት፣ በተንኮልና በዕውቀት አስተሳሰብ አድማስ ደካማ ስለሆኑ የዜጎችን አንድነትና ብሔራዊነት ስሜትን አጥብቀው ይጠላሉ፤ ይህንንም በማሰራጨት የማሃይሞችን ርካሽ ፖለቲካ አራምደውበታል፣እያራመዱም ይገኛሉ፡፡ የዚህ ዋነኛ ተባባሪ ደግሞ በህወሓት የሚነዱት ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የሀገሪቱን አንድነትና ደህንነት አደጋ ላይ በመጣላቸው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዝምታ ሊያልፍ ስለማይገባ እስካሁን ለፈፀሙት ሁሉ አስፈላጊውን ሰነድ በእጃችን ማስገባት፣ ድርጊቱን የፈፀሙትንና ተባባሪዎቹን ስም ዝርዝር ከነ ሙሉ አድራሻቸው መያዝ፣ ጉዳት የደረሰባቸውና ሚደርስባቸው ዜጎችን መርዳትና መንከባከብ እንዲሁም ወንጀለኞችን በተለያዩ ማኀበራዊ ሚዲያዎች(Facebook, blog, twitter,….) ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በማጋለጥ ለህግ እንዲቀርቡና ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ የሁላችንም ኢትዮጵያዊያን የውዴታ ግዴታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ዛሬ በሰፊው የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ በህወሓት/ኢህአዴግ እየደረሰ ያለው ግፍ በተመሳሳይ መልኩ ነገ በሌሎችም ላይ ይደርሳል፤ ከዚህ በፊትም ደርሷልና፡፡

Saturday, April 6, 2013

የመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የሚደርስባቸውን ግፍና በደል ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ (IOM)አስታወቀ:


  • ከኢትዮጵያ ሰሜን ምስራቅ ወገኖቻችን ለኤደን ባሕር አሳ አዞ ገብረው ቀይ ባህርን የተሻገሩ ኢትዮጵያውያን ስቃይ ሰቆቃ እንስማ ::
የመን ከነዓን ጩኧቱ ይቀጥላል::የመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የሚደርስባቸውን ግፍና በደል ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ዓላም አቀፉ ድርጅት የስደተኞች መርጃ ድርጅት (IOM)አስታወቀ:: ዓለም ድርጅቱ እንደሚለው በተለይ የመንን የሳውዲ አረቢያ ጋር በሚያዋስነው አካባቢ የሰፈሩ ስረተኞች ከምግብና ከመጠለያ ባለፈ ችግር በወረበሎች እየታገቱ የሚደርስባቸው ግፍ ከሚነገረው በላይ ነው::በኢትዮጵያ IOM የመገናኛ ጉዳይ ባለሙያ አቶ ደምሰው ብዙወርቅ እንደሚሉት መውሪያ ቤታቸው ስደተኞችን ለመርዳት ቢሞከርም በገንዘብ እጥረትና በስደተኞች ቁጥር መብዛት ምክንያት ተፈላጊውን ርዳታ መስጠት አልተቻለም::
ወደ ሰሜን አፍሪካ እስከ ሊቢያ ፥ ሽቅብ እስከ ሜድትራኒያን ማዶ እስከ ሞልታ ወይም ኢጣሊያ ደግሞ በተቃራኒው ቁልቁል ወደ ደቡብ አፍሪቃ እስከ ታንዛኒያ ፥ ማላዊ ፥ ሞዛምቢክ ወይም ደቡብ አፍሪቃ ጥግ እስ_ ቢሉ የኢትዮጵያውያን ፥ የኤርትራና የሱማሌ ስደተኞች ስቃይ ሰቆቃ እስኪያንገቸሸግሽ ይሰማሉ::

ገረብ ገረብ ትግራይ መቃብር አምሃራይ


ገረብ ገረብ ትግራይ መቃብር አምሃራይ

ቴዎድሮስ ሐይሌ (tadyha@gmail.com)
አንካሳ በምርኩዝ እውሩ በመሪ የተከተልዎ፤
እህል አይበቅልም ወይ ንጉስ በአገርዎ፤
በጽዮኗ እመቤት በጭንቅ አዛኝዎ፤
በቅዱስ ሚካኤል በጋሻ ጃግሬዎ፤
ጎጃምን ይማሩት ፈሪም አንልዎ።
ከታላቁ ንጉስ አጼ ቴዎድሮስ ሞት በኋላ የነገሱት የትግራዩ መሳፍንት ወገን የሆኑት አጼ ዮሃንስ ንግስናቸውን ለማጠናከር ጎጃምን በወረሩ ግዜ ታሪክ እንደሚለው ተከታይ ሰራዊታቸው የሃገሬውን ሃብት በጎተራ ያለ እህል በበረት ያለ መንጋ ከብት በሜዳ ላይ የነበረ ክምርና ያልታጨደ ሰብል ሳይቀር ያለ ምህረት ሙልጭ አርጎ በመዝረፍ ህዝቡንም በከባድ የአካልና የሞት ቅጣት በመፈጸም ያካሄዱትን ከፍ ያለ መከራ የተመለከተ ከስቃይ ያመለጠ ገጣሚ ያቀረበው ቁጣና ተማጽኖ ነበር።

Ethiopia’s Human Rights Crisis Worsened


  • Ethiopia’s Human Rights Crisis Worsened

Betre Yacob Ethiopian Journalist and blogger
by Betre Yacob
The human rights situation in Ethiopia, the most important strategic and security ally of the Western powers, has worsened drastically, according to the 2013 Human Rights Watch’s World Report, which summarizes the human rights situation of more than 90 countries worldwide—drawing on events from the end of 2011 through November 2012.
The 665 page report says that Ethiopia’s dictatorial regime has deliberately continued to severely restrict fundamental rights of freedom of expression, association, and assembly. In addition, the report indicates that intimidation, arbitrary arrest, torture, forced displacement, and killing remain routine throughout the country.

ለዜጎች መሞት፣ መፈናቀልና መሰደድ ተጠያቂው መንግስት ነው!!!


ለዜጎች መሞት፣ መፈናቀልና መሰደድ ተጠያቂው መንግስት ነው!!!


  1. አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ


አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
  1. UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

ወንጀለኞች በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን
በተደጋጋሚ ፓርቲያችን እንደሚገልፀው አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት የሚከተለው ቋንቋን መሰረት ያደረገ ፌደራሊዝምና የስርዓቱ አራማጆች ካላቸው የስልጣን እድሜን የማራዘም ጉጉት ተደማምረው ለሃገራችን እንዲሁም ተቻችሎ፣ ተዋልዶ፣ ተዛምዶና ተዋድዶ ለዘመናት ይኖር ለነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ግልፅና አስፈሪ አደጋ ወደ መሆን እንደደረሱ በግላጭ እየታየ ነው፡፡ለዜጎች መሞት፣ መፈናቀልና መሰደድ ተጠያቂው መንግስት ነው!!!
ያ ለዘመናት አብሮን የቆየው በጋራ የመኖር ዕሴት እየተደመሰሰ በምትኩ የሚያጋጩ ስልቶች እየተፈጠሩና እየተተገበሩ ወደ ሰቆቃ ተለውጠው ይገኛሉ፡፡ የዜጎች ሰዋዊና ህጋዊ መብት እየተጣሰም ነው፡፡ በኢትዮጵያችን ውስጥ አብሮ የመኖር፣ ከቦታ ቦታ የመዘዋወርና በፈለጉት ቦታ ሃብት የማፍራት ህልውና እያከተመ መጥቷል፡፡ ለዚህ ክፉ ድርጊት ተጠያቂ የሚሆነው ደግሞ የዜጎችን መዘዋወር መብትና ሃብት የማፍራት መብት ማረጋገጥ የተሳነው መንግስትና መንግስት ብቻ ነው፡፡
የከዚህ በፊቱን የማፈናቀል ግፍ ትተን በቅርቡ እንኳ በጉረፈርዳና በሌሎች አካባቢዎች በቀጥታ በክልሉ ባለስልጣናት በተፃፈ ደብዳቤ ይሄ ሀገራችሁ አይደለም ተብለው፣ ሃብትና ንብረታቸው ተዘርፎ፣ የወለዱ አራሶች እንኳን የማገገሚያ ጊዜ ሳይሰጣቸው ደማቸውን እያዘሩ ሲባረሩ ከመንግስት የተሰጠው ምላሽ ‹‹ሞፈር ዘመቶች ናቸው (ማረሻውን ብቻ ተሸክሞ ወደ ሌላ ሀገር የሚሰደድ ለማለት ይመስለናል)›› የሚል ነበር፡፡ ይሄም ቢሆን የማንኛውም ዜጋ መብት ነው፡፡ መንግስት እነዚህ ዜጎች ‹‹ሃገራችን የት ነው?›› በማለት ለሚያነሱት ጥያቄ መልስ የለውም፡፡

Monday, April 1, 2013

ወያኔን ማመን ቀብሮ ነው ፡


ወያኔን ማመን ቀብሮ ነው



አምባገነን መንግስታት አገዛዛቸውን ለማቆየት ከሚጠቀሙበት ዋነኛ መሳሪያቸው ከሆነው የጦርና የደህንነት ሃይል ውጭ በርካታ ዘዴዎችን ይጠቀማሉ። ልዩነትን ማራገብና ህዝብን መከፋፈል፣ ማስፈራራት፣ ዜጎች መረጃ እንዳያገኙ አማራጭ ሚዲያዎችን ሁሉ ማፈንና መዝጋት ብሎም የጥቂቶቹን ስብእና በጥቅማጥቅም  በመግዛት ሎሌና ጋሻ ጃግሬ በማድረግ፤ እንዲሁም በአገዛዛቸው የተማረረውን ህዝብ የተስፋ ዳቦ ላያድሉት እየጋገሩ ነገ የተሻለ ቀን ይመጣል እያሉ መስበክ ከብዙ ጥቂቶቹ ዘዴዎቻቸው ናቸው።
የሰሞኑን የወያኔ ጉባኤና ያወጣቸውን መግለጫዎች ልብ ብሎ የሚያጤን ኢትዮጵያዊ ሁሉ አንድ ነገር በግልጽ ማየት ይችላል። እሱም የጉባኤዉ ተሳታፊዎችና የወያኔ/ኢህአዴግ መሪዎች የሚጋሩት፤ አብሮ ያቆማቸዉና ከምንም በላይ የሚያያይዛቸው አንድ ነገር ቢኖር ፍርሃታቸው መሆኑ ነው። በአለም ዙሪያ በከፍተኛ ፍጥነት እየናኘ አምባገነኖችን እንደማእበል ከወዲያ ወዲህ እያናወጠ፣ እየጠራረገ በማስወገድ ላይ ያለው የህዝብ የዴሞክራሲና የሰበአዊ መብት መከበር ጥያቄ፣ የእነሱንም በር እያንኳኳ መሆኑ ከፍተኛ ፍርሃት ለቆባቸዋል።
እነዚህ ዘረኛ ቡድኖችና ግፈኞች የሚጋሩት ህዝባዊነት ያለው መርህና የሀገር ራእይ የላቸውም። ለዚህም ነው ጉበኤያቸዉን ሞቶ በተቀበረ ሰዉ መሪ ቃል ጀምረዉ በዚሁ በሞተ ሰዉ ራዕይ የጨረሱት። የዚህ ሰዉ ራዕይ ደግሞ ዘረኝነት፤ስደት፤ እስር፤ ግድያ፤ንቀት፤ዘለፋና ህዝብን ማዋረድ ነዉ። የኢህአዴግ/ወያኔ መሪዎች የሚያስተዉል አዕምሮ ስለሌላቸዉ አልተረዱትም እንጂ ለኢትዮጵያ ህዝብ በዚህ በዘጠነኛ ጉባኤያቸዉ በግልጽ የነገሩት ነገር ቢኖር ፓርቲያቸዉ ኢህአዴግ የራሱ የሆነ ራዕይ የሌለዉ ጭራሽ በሞተ ሰዉ ራዕይ የሚንቀሳስ ሙት ፓርቲ መሆኑን ነዉ።