ከኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የጋራ እንቅስቃሴ አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ
ኢትዮጵያ የብዙ ብሔረሰቦችና ሀይማኖት ተከታዮች ሀገር ናት። እነዚህ ብሔረሰቦች ለብዙ ዘመናት በአንድነትና በሕብረት ተደጋግፈው፤ ተጋብተውና ተስማምተው ኖረዋል። ከውጭ የመጣባቸውን ጠላትም በተባበረ ክንዳቸው መክተው በመመለስ በዓለም ታዋቂ ታረክ አስመዝግበዋል። በአሁኑ ወቅት ከመሀከላቸው የበቀሉ ተንኮለኞች ለፓለቲካ ሥልጣንና ለግል ጥቅም ማራመጃ ሲሉ የሚያካሂዱትን የመከፋፈል እርምጃ የኢትዮጵያ ሕዝብ በተከታታይ እያከሸፈው ቢሆንም፤ በአሁኑ ወቅት በጦር ኃይል እያስገደዱ በአንድ ብሔረስብ ላይ ያተኮረ አስከፊና አደገኛ የዘር ማጥፋት ተግባር እያከናወኑ ይገኛሉ።
ይህንን ሰላም ወዳድና በሰላም የኖረ ሕዝብ እርስ በራሱ በማጋጨትና አንዱ በአንዱ ላይ እንዲነሳሳ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ ግንባር/ሕወሓት መሪዎች ከፅንሳቸው ጀምረው በፖሊሲ ደረጃ ነድፈው እስካሁን በማስፈጸም ላይ ይገኛሉ። ወደፊትም በሥልጣናቸው ለመቆየትና ከሕዝብ የሚዘርፉትን ንብረት ካለምንም ተቃውሞ ለማካሄድ ወገኖቻችንን በዘርና በቋንቋ በመለያየት ለዘመናት ከኖሩበት አካባቢ ጭካኔ በተመላበት ሁኔታ ሆን ተብሎ በተቀየስ የዘር ማጥራት ፖሊሲ አማካኝነት ለጊዜው ከተወሰኑ ክልሎች በማፈናቀል ላይ ናቸው።