Sunday, June 30, 2013

…. ትንሽ ስለ ጀዋር መሓመድ ……በአብርሃ ደስታ

አንድ ጓደኛየ አንድ የተቀናበረ ቪድዮ በፌስቡክ ገፄን ለጠፈልኝ፤ እንዳነበው እየጋበዘኝ መሆኑ ነው። ቪድዮው ስለ ጀዋር ነው። ግን የሌሎች ሰዎች ስሞችም (የኔን ጨምሮ) ተጠቅሷል። ልጁ ቪድዮውን ሲጋብዘኝ አንዳንድ ዲያስፖራ ተቃዋሚዎች ስለኔ ያላቸው አመለካከት እንዳውቅና ኢህአዴግ መቃወሜን እንዳቆም ‘በአሪፍ’ ተፅዕኖ ማሳደሩ ነው፤ ይህን ድምዳሜ የመጣልኝ ልጁ (ቪድዮው የላከልኝ) ከዚህ በፊት ይልክልኝ በነበሩ ተመሳሳይ መልእክቶች በመነሳት ነው። ይህን የፖለቲካ ስትራተጂ እንደማይሰራ በተደጋጋሚ ለማረጋገጥ ሞክርያለሁ።
ግን …
ሰዎች በኔ ሓሳብ ሊደሰቱ ወይ ሊናደዱ ይችላሉ፤ መደሰትም መናደድም መብታቸው ነው። እኔ ደግሞ የፈለኩትን የመፃፍ መብት አለኝ። ስለዚህ የኔ አቋም ሌሎች ሰዎች በሚሰጡኝ ምላሽ የተንጠለጠለ አይደለም።
ወደ ጀዋርና ቪድዮው ልመለስ። ቪድዮው ጀዋርና ሌሎች ሰዎች ስለተናገሩት ሓሳብ ቀነጫጭቦ ያቀርባል። በመጀመርያ ቪድዮው ትኩረት አልሰጠሁትም ነበር። በኋላ ስለ ቪድዮው የተፃፉ ነገሮች ሳነብ ግን ትኩረት እንደሚያስፈገው ገባኝ።
ባጠቃላይ ሲታይ የተቀናበረውን ቪድዮ አልወደድኩትም። አንደኛ የተቀመጠው የጀዋር ሓሳብ የተቆራረጠ ነው። ለድምዳሜው የሰጣቸው ማስረጃዎች በትክክል በቪድዮው አልተካተቱም። አንድ ጥሩ የነበረ ሓሳብ ቆራርጠን በማቅረብ ጥላሸት መቀባት ይቻላል። ስለዚህ ጠቅላላው የቀረበ አመክንዮ በተፈለገው መጠን ስላልቀረበ በቪድዮን በቀረቡ የተቀነጫጨቡ ሓሳቦች መገምገም አንችልም።
ሁለተኛ በቪድዮው የቀረበው የተቀነባበረ ሓሳብ ጀዋርን ለመገምገም ያስችለናል ብለን ከተነሳን የተናገረው ነገር የልጁን ስም ለማጥፋት በቂ ምክንያት ይሆናል ወይ? የሰጠው ሓሳብ የራሱ (የግሉ) አስተያየት ነው። ‘ኦሮሞዎች በደል ይደርሳቸው ነበር’ ብሎ ማለት ‘ኢትዮዽያን መጥላቱ’ ያሳያል ወይ? የብሄር ጭቆና መኖሩ ሓሳብ መሰንዘር ‘ኢትዮዽያዊ ስሜት’ እንደሌለው ምክንያት ወይ ማረጋገጫ ሊሆን ይችላል ወይ?
ስለ ኢትዮዽያ ስናወራ ስለኢትዮዽያውያን እየተናገርን ነን። ኢትዮዽያውያን ህዝቦች ናቸው። ህዝቦቹም ኦሮሞዎች፣ አማራዎች፣ ትግራዮች፣ ጉራጌዎች፣ ሶማሊዎች፣ ደቡቦች፣ ጋምቤላዎች፣ ቤኑሻንጉሎች … ወዘተ ናቸው። ‘ጉራጌ ተበደለ’ ሲባል ኢትዮዽያዊ እየተበደለ ነው ማለት ነው። ስለዚህ ጀዋር ‘ኦሮሞች ተበድለዋል’ በማለቱ የተፈጠረ ችግር ምንድነው??? እንኳንም በድሮ ዘመን አሁንም እኮ ‘ጭቆና አለ’ ብለን እየተከራከርን ነን።
ሦስተኛ ጀዋር የሰጠው አስተያየት ጥሩ አይደለም ብለን እንነሳ፤ ታድያ ማድረግ ያለብን ጉዳይ ስም ለማጥፋት መሯሯጥ ሳይሆን አስተያየቱ ስህተት መሆኑ በሓሳብ ማሳመን መቻል ነው። በሰጠው አስተያየት ላይ የሓሳብ ክርክር መክፈት ይቻላል። አስተያየቱ ‘ስህተት’ ስለመሆኑ ማረጋገጥ የምንችል ከሆነ ጀዋርን ለማስተካከል እንዴት ያቅተናል?
አራተኛ አንድ ሰው የተለየ አስተያየት ስለሰጠ ‘የኢትዮዽያ ጠላት’ አድርጎ መፈረጅ መፍትሔ ይሆናል ወይ? ሁሉም ሰው ስለ አንድ ጉዳይ ተመሳሳይ አቋም ይኖረው ዘንድ ግድ አይደለም። የምንታገለው አንድ ዓይነት አስተሳሰብ እንዲኖረን ለማድረግ ሳይሆን እንደየምርጫችን በነፃነት መኖር እንድንችል ነው።
በመጨረሻም
ጀዋር በያዘው አቋም ልዩነት ቢኖረኝም በሰጠው አስተያየት ግን አልተከፋሁም፤ ጥፋቱም አልገባኝም። የብሄር ጭቆና እንደነበር (አሁንም ችግሩ በተገቢ መንገድ እንዳልተፈታ) ከጀዋር ጋር እስማማለሁ። በአሁኑ ሰዓት (ችግሩ ለመፍታት) ምን መደረግ አለበት በሚለው (ብሄርን ከሀገር ማስቀደሙ) ግን ከጀዋር ጋር የሓሳብ ልዩነት አለኝ።
እንደኔ ከሆነ የዘመናት የፖለቲካ ችግሮቻችን መፍታት የምንችለው ታሪክን እያስታወስንና ብሄርን እያስቀደምን የሀገራችን አንድነት በሚያዳክም መልኩ በመወያየት ሳይሆን የነበረው ጭቆና እንዲወገድ አብረን በመታገልና በእኩልነትና በአንድነት የምንኖርባት ኢትዮዽያ እውን በማድረግ ይመስለኛል።
ጀዋር መሓመድ በጣም ከማደንቃቸው ብርቅዬ ወጣት ኢትዮዽያውያን የፖለቲካ ተንታኞች አንዱ ነው። ጀዋር አድናቆቴን ይድረሰህ።
በሓሳብ መለያየት ጥፋት አይደለም። ስለዚህ የሰው ስም ለማጥፋት ዘመቻ መክፈት ተገቢ አይደለም።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመጀመሪያው ጋዜጣዊ መግለጫ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመጀመሪያው ጋዜጣዊ መግለጫ

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፣ የተኳቸው የኢሕአዴግ መራሹ መንግሥት ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሥልጣን ላይ በወጡ በዘጠነኛ ወራቸው ከአገር ውስጥ ጋዜጠኞች ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ በመገናኘት፣ በአጠቃላይ የአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባለፈው ዓርብ ማለዳ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
“ጥያቄ ለማቅረብና ማብራሪያ በመሻት በመምጣታችሁ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡ ከዚሁ ቀጥሎ የምትፈልጉትን ጥያቄ እንደትጠይቁ ዕድል እሰጣለሁ፤” በሚል የመግቢያ ንግግር ጋዜጣዊ መግለጫውን የጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለሁለት ሰዓት ከ15 ደቂቃ የፈጀ ቆይታ ከጋዜጠኞች ጋር አድርገዋል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ የተገኙ ከ20 በላይ ጋዜጠኞች ያገኙትን ዕድል በመጠቀም በአገሪቱ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ በተለይም በቅርብ በተከሰተው የዓባይ ግድብ ውዝግብ፣ በሙስናና በሌሎች ጉዳዮች ላይ በርካታ ጥያቄዎችን በማቅረብ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ዝርዝር ምላሽ ሰምተዋል፡፡ በዋና ዋና አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት ማብራሪያ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ኢኮኖሚያዊና ተያያዥ ጉዳዮች
ከ2005 ዓ.ም. አጋማሽ በኋላ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ የአክሲዮን የንግድ ድርጅቶች ላይ የጣለው የዲቪደንድ ታክስ (የትርፍ ድርሻ ክፍፍል ላይ የሚጣል ታክስ) ጉዳይ በመጀመሪያ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበ ጥያቄ ነበር፡፡
የአገሪቱ የታክስ ሕግ የተጠቀሰውን የታክስ ዓይነት አስመልክቶ በተከፋፈለ የአክሲዮን ድርሻ ትርፍ ላይ የአሥር በመቶ ታክስ የሚጥል መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ በአክሲዮን የተቋቋሙ ድርጅቶች በአጠቃላይ የአሥር በመቶ ታክሱን የትርፍ ድርሻ ክፍፍል አደረጉም አላደረጉም በአጭር ጊዜ ሊከፍሉ ይገባል በሚል ባወጣው መመርያ፣ የንግዱ ኅብረተሰብን ሲያጉላላና ሲያከራክር ቆይቷል፡፡ ታክስ ባለሥልጣኑ ባወጣው መመርያ መሠረት ድርጅቶቹ የተጠቀሰውን ታክስ ወደኋላ ለአምስት ዓመታት በማስላት እንዲከፍሉ በመወሰኑ የተነሳ፣ ድርጅቶቹ በጉዳዩ ላይ ያነሱት የሕግ ጥያቄ ሳይመለስ ቅጣትን ፍራቻ ክፍያ እየፈጸሙ ይገኛሉ፡፡ የዚህን ታክስ አግባብነት የተጠየቁት አቶ ኃይለ ማርያም ተከታዩን ብለዋል፡፡
“ከትርፍ ድርሻ የሚከፈል ታክስ የሚጠየቀው የትርፍ ድርሻው ከተከፈለ ብቻ ነው፡፡ የትርፍ ድርሻው ሳይከፋፈል ለኢንቨስትመንት ከዋለ ታክስ አይከፈልበትም፡፡ ይህ የቆየ የመንግሥት አቋም ነው፤” ብለዋል፡፡
በታክስ ባለሥልጣኑና በንግዱ ኅብረተሰብ መካከል የተፈጠረው ክርክር የትርፍ ድርሻው ተመልሶ ለኢንቨስትመንት ውሏል? በሚል ጥያቄ ላይ መሆኑን አቶ ኃይለ ማርያም ከገለጹ በኋላ፣ መጣራት ያለበት የትርፍ ድርሻው ለባለሀብቶች ተከፋፍሏል ወይስ ለኢንቨስትመንት ውሏል የሚለው እንደሆነና ይህ እየተሠራ መሆኑን አሳውቀዋል፡፡
ስህተቱን የሠራው መንግሥት መሆኑ ከተረጋገጠ በንግዱ ኅብረተሰብ ላይ ለደረሰው መጉላላትና ጥቅም ማጣት መንግሥት ይቅርታ ይጠይቃል? የሚል ተያያዥ ጥያቄ ቀርቦላቸው፣ “ስህተት መኖሩን ካረጋገጥን ይቅርታ የማንጠይቅበት ምክንያት የለም፤” ብለዋል፡፡
ጉዳዩ አከራካሪ እንደሆነ በመጠቆምም አንዳንዱ ትርፉን ተቀብሎ መክፈል የማይፈልግ መኖሩን፣ ነገር ግን ለኢንቨስትመንት የዋለም እንደሚገኝ እንደሚገነዘቡና ይህንን ማጣራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ዕድገት ዙሪያ ከዚህ ቀደም ሲጠራጠሩ የነበሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ዕድገቱን ወደ መቀበል መምጣታቸውን፣ ነገር ግን እንደ የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ያሉ ተቋማት አሁንም የሚያወጧቸው መረጃዎች አሉ፡፡ ለአብነትም ዘንድሮ ይመዘገባል ብለው የገመቱት የኢትዮጵያ ዕድገትና የመንግሥት ግምት አሁንም የተለያዩ መሆናቸውን በተመለከተ፣ መንግሥትም ሌሎች ተቋማትም የሚግባቡበት በኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ኢንቨስትመንት መኖሩንና በዚህ መሀል የገንዘብ ፖሊሲውን በማጥበቅ የዋጋ ንረትን መዋጋት የሚለው የመንግሥት አቋም ግጭት የለበትም ወይ? እንዲሁም ባለፈው ዓመት የታየው የግብርና ምርት ዝቅተኝነት፣ በተመሳሳይም የኢንዱስትሪው ዘርፍ ዝቅተኛ አፈጻጸምን ከግምት በማስገባት ባለ ሁለት አኀዝ ዕድገት ዘንድሮ መጠበቅ አይከብድም ወይ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡
በሰጡት ምላሽም፣ “ላለፉት 11 ዓመታት በአይኤምኤፍና በኢትዮጵያ መንግሥት የዕድገት ትንበያ ዙሪያ ልዩነቶች ነበሩ፡፡ ወደ ትክክለኛው መረጃ ስንመጣ ግን የእኛን መረጃ ሲያስቀምጡ ነው የኖሩት፡፡ የለመድነው ነገር ዛሬ ቢደገም ምን አዲስ ነገር አለው፤” ብለዋል፡፡ በማከልም፣ “ግምት ግምት ነው ግምቱ ወደ እውነት መጠጋት ግን አለበት፤” በማለት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ግምት ሁሌም ወደ እውነት የተጠጋ እንደነበርና አሁንም እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
ባለፈው ዓመት 8.5 በመቶ ዕድገት እንዲመዘገብ ምክንያት የሆነው ግብርናው ያሳየው የ4.9 በመቶ ዝቅተኛ አፈጻጸም መሆኑን፣ በዚሁ ዓመት ተስተውሎ የነበረው የኢንዱስትሪ ዘርፍ ዝቅተኛ አፈጻጸም የመነጨው በጥቃቅንና አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገት ወደ 13 በመቶ በመውረዱ እንጂ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በ18.6 በመቶ አድጎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
የጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ያሳየው ዝቅተኛ አፈጻጸም አጠቃላይ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ወደኋላ እንደሳበው፣ ነገር ግን መንግሥት ካለፈው ዓመት ጀምሮ በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ላይ በወሰደው ዕርምጃ ውጤት በመታየቱ፣ ከዚህ ባለፈም የግብርና ዘርፍ የሰብል ምርት ዕድገት ብቻ ስድስት በመቶ ማደጉንና ከስታስቲክስ ባለሥልጣን የተገኘው መረጃ ከሌሎቹ የግብርና የዘርፍ ዓይነቶች ዕድገት ጋር ሲደመር፣ ቢያንስ የግብርና ዕድገቱ ሰባት በመቶ ስለሚሆን ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የመንግሥት ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እያለ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር የሚለውን በተመለከተ ምላሽ የሰጡት፣ ከዋጋ ንረት ጋር በተያያዘ ሁለት ዓይነት አስተሳሰቦች መኖራቸውን በማስቀደም ነበር፡፡
“አንደኛው ዕድገት እያስመዘገቡ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር ሲሆን፣ ሁለተኛው ዕድገትን ገቶ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር ይገባል የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ ይህ ሁለተኛው አስተሳሰብ በምሥራቅ እስያ አገሮች ልምድ አልሠራም፡፡ ዕድገት እየመጣም የዋጋ ንረትን ተቆጣጥሮ መሄድ ይቻላል የሚለው በተግባር የተረጋገጠ ነው፡፡ በእኛም ሁኔታ ዕድገት እያስቀጠልን የዋጋ ንረትን ማውረድ ችለናል፤” ብለዋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት በሰጡት ማብራሪያ ዋናው ነገር የዋጋ ንረቱ ምንጭ እንደየአገሩ የሚለያይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ባደጉ አገሮች ያለው የዋጋ ንረት ምንጭና ግፊት ባላደጉ አገሮች ካለው ጋር ፈጽሞ እንደሚለያይ ተናግረዋል፡፡
“የእኛ መነሻ ምንድን ነው? የእኛ የምግብ ዋጋ ንረት ነው መነሻው፡፡ ዋናውና ትልቁ የግብርና ምርት ላይ ትንሽ ፈቅ ሲባል ዋጋው ይወርዳል፡፡ አርሶ አደሩ ዋጋ ወደቀ ብሎ መንጫጫት ይጀምራል፡፡ ስለዚህ መነሻው እንጂ አጠቃላይ ቲዎሪው አይደለም የሚወስነው፤” ብለዋል፡፡
ገንዘብ ወደ ኢኮኖሚው ውስጥ ሲገባ የሚያመጣው የዋጋ ግሽበትና በአቅርቦት ምክንያት የሚመጣውን ግሽበት መንግሥት ከፋፍሎ መመልከቱን አቶ ኃይለ ማርያም የገለጹ ሲሆን፣ “ገንዘብ በኢኮኖሚው ውስጥ በሚገባበት ወቅት ግሽበት አይፈጥርም ሳይሆን፣ አቅርቦት በሚጎልበት ወቅት የዋጋ ንረቱ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚጨምር አይተናል፡፡ ስለዚህ አቅርቦቱን በማሻሻል የዋጋ ንረቱን መቆጣጠር ይቻላል፤” በማለት አስረድተዋል፡፡
በማጠናከርም ግሽበትን ለመፍታት አቅርቦቱን ማሻሻል ማለት በሌላ በኩል ግብርናን ማሳደግ መሆኑንና ይህም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንደ መግደል እንሚቆጠር በመግለጽ ይህ ሊሆን የቻለው ከኢኮኖሚያዊ አወቃቀሩ የተነሳ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
የግብፅ ጉዳይ
በኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምክንያት የኢትዮጵያና በግብፅ መካከል ስለተከሰተው አለመግባባትና ችግሩን ለመቅረፍ ያለው ዕድል፣ የሁለቱ አገሮች አለመግባባትን ተከትሎ በግብፅ በኩል ስለታየው የጦርነት ጉሰማ አካሄድና የባለሙያዎች ቡድን ያቀረበውን ሪፖርት በተመለከተ ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት አስተያየት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ተፋሰሱን በጋራ የመጠቀም ፅኑ እምነትን አጉልተው አንፀባርቀዋል፡፡
“ፍላጎታችን በጋራ ብልፅግና ላይ የተመሠረተ ትብብር ይኑር የሚል ነው፡፡ ይህ አቋማችን ይቀጥላል፡፡ ይህንን አቋም የዓለም ኅብረተሰብ በአጠቃላይ እየተቀብለው ነው፤” ብለዋል፡፡
ሰጥቶ በመቀበል መደራደር ላይ የተመሠረተ አቋም በኢትዮጵያ በኩል መኖሩን በመግለጽ፣ የባለሙያዎቹ ቡድን ያቀረበው ሪፖርት ግድቡ የተፋሰሱን አገሮች ሊጠቅም እንደሚችል ያለማወላዳት እንዳስቀመጠ ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ የቡድኑ ሪፖርት ሌሎች የሰጣቸው የመፍትሔ ሐሳቦች መኖራቸውን ከዚህም ውስጥ የግድቡ ዲዛይንን እንደሚመለከት ገልጸዋል፡፡
ይህንንም ሲያብራሩ የግድቡ ኮንትራት የኢንጂነሪንግን ግዥና ግንባታን ያጠቃለለ መሆኑን፣ ይህም ማለት የመጀመሪያው ዲዛይን ብቻ ተሠርቶ ቀጣይ ዙር ዲዛይኖች በዚህ ላይ መሠረት ተደርገው እንደሚሠሩ፣ በመሆኑም ቀጣይ ዲዛይኖች ላይ መካተትና ሊተኮርባቸው የሚገባቸውን ሐሳቦች ባለሙያዎች በሪፖርታቸው እንዳቀረቡ ገልጸዋል፡፡
“የእኛ መንግሥት ከቀረቡት ሐሳቦች ውስጥ እጅግ አብዛኞቹን በአሁኑ የሥራ ወቅት በዲዛይኑ እያካተተ የሄደበት ሁኔታ አለ፡፡ ስለዚህ አስተያየቶቹን ለማካተት ቆም ብለን እንነጋገራለን የሚል ስምምነት ከግብፅ ጋር ተደርሷል፤” ብለዋል፡፡
ሌላው የባለሙያዎቹ ቡድን ግድቡ ሊፈጥር የሚችለው የአካባቢ ተፅዕኖ መጠናት ያለበት መሆኑን እንደጠቆመ የገለጹት አቶ ኃይለ ማርያም፣ “ግብፅና ሱዳን በዚህ ረገድ መረጃ ሊሰጡ ፈቃደኛ ስላልነበሩ ባለን መረጃ ላይ ብቻ ተመሥርተን ነው የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናቱን ያካሄድነው፤” በማለት በዚህ ጉዳይ ላይም ተነጋግሮ መሥራት እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ግብፅ ለመደራደር ዝግጁ መሆኗ ጥሩ ነገር እንደሆነ ነገር ግን ውጤቱን መተንበይ እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡ በድርድሩ ወቅትም ሆነ በማንኛውም ጊዜ ቢሆን፣ “የግድቡ ሥራ የማይቆም መሆኑንና መጠኑ የማይቀንስ መሆኑም መታወቅ አለበት፤” ሲሉም የመንግሥታቸውን አቋም ግልጽ አድርገዋል፡፡
የግብፅ ፕሬዚዳንት ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በግድቡ ዙሪያ በመወያየት በግልጽ በሚዲያ የታየው ኢትዮጵያን የማተራመስ አቋም ሆን ተብሎ ይሆን በስህተት ባይታወቅም፣ ከ120 ዓመታት በፊት ጀምሮ በግብፅ ይራመድ የነበረ አስተሳሰብ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
“በዚህ አስተሳሰብ መመራት ትክክል እንዳልሆነ ለግብፅ መሪ በተደጋጋሚ ገልጫለሁ፡፡ መንግሥታቸው ይህንን አቋም ይዟል የሚል እስካሁን አልሰማንም፤ ይህንን አቋም በያዘ ጊዜ ግን አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይገባሉ ማለት ነው፤” ብለዋል፡፡
የሙስና ጉዳይ
በቅርቡ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣናትና ባለሀብቶች በሙስና ተጠርጥረው መያዛቸውን ተንተርሶ፣ በኢሕአዴግ የፖለቲካ ልዩነት የተነሳ የተወሰደ ዕርምጃ ስለመሆኑና በቀጣይ የመንግሥት ተመሳሳይ ዕርምጃዎች ላይ ተጠይቀው በሰጡት ማብራሪያ፣ ዕርምጃው በኢሕአዴግ ጉባዔ እንዲሁም በማዕከላዊና በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ደረጃ ጥልቅ ውይይት ተካሄዶበት የተያዘ አቋም መሆኑን ገልጸዋል፡፡
“ኪራይ ሰብሳብነትን አንዳንዶች እስከሚያሾፉበት ድረስ እየተነገረ ያለ ቃል ነው፡፡ ይህንን ዕውን በማድረግ የድርጅታችን አንድነት፣ የመንግሥትና የሕዝብ ጠላት መታገል አለብን ብለን ነው ያስቀመጥነው፤” ሲሉ አክለዋል፡፡
የሙስና ሥራ የሰዶ ማሳደድ ሥራ ባለመሆኑ በተጠና መንገድ ሥራ መጀመሩን፣ በዋነኛ ደረጃ ከተለዩት ውስጥ የመሬት አስተዳደር ሥርዓቱ ላይ በተወሰደ ዕርምጃ ግለሰቦች ተጠያቂ እንደተደረጉ ገልጸዋል፡፡
ሙሰኞችን መቅጣት ብቻ ሙስናን መዋጋት አይደለም፡፡ ሥርዓቱ ለሙስና ምቹ እንዳይሆን ማድረግ ይገባል ከሚል ፅኑ እምነት በመነሳት የመሬት ሥርዓቱን የማስተካከሉ ሥራ መካሄዱን ተናግረዋል፡፡
“በሁለተኛ ደረጃ ታክስ ላይ መጥተናል፡፡ ቢሮክራሲውንም ከፍተኛ አመራሩንና ባለሀብቶችን ተጠያቂ አድርገናል፤” ብለዋል፡፡ “የፖለቲካ ልዩነት ስላለ ነው በሚል ለቀረበው ጥያቄ ይህንን ሊል የሚችል ካለ የፖለቲካ ልዩነት ሳይሆን የመቀራረብ ልዩነት ነው፡፡ ከሙሰኞች ጋር የተቀራረበ ካለ ደስ ሊለው ይችላል ብሎ መውሰድ አይቻልም፡፡ ….. ከየቤታቸው በሻንጣ የተከማቸ ገንዘብ እየወጣ እየታየ ምን የፖለቲካ ልዩነት ሊባል ይችላል?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ቀጣዩ መንግሥት ያተኮረበት የሙስና ምንጭ የመንግሥት ግዥ ዘርፍ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ኃይለ ማርያም፣ “ይህ አገር ከፍተኛ የመሠረተ ልማት እያካሄደ ነው፡፡ ከውጭ ባለሀብቶች ጋር ከፍተኛ የኮንትራት ስምምነትና ድርድሮች የሚደረግበት ነው፡፡ በመሆኑም የሙስና ምንጭ ነው፡፡ ስለዚህ በጥናት ላይ የተመሠረተ የመፍትሔ ዕርምጃ እንወስዳለን፤” ሲሉ ቀጣይ ዘመቻቸውን ጠቁመዋል፡፡
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፣ የተኳቸው የኢሕአዴግ መራሹ መንግሥት ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሥልጣን ላይ በወጡ በዘጠነኛ ወራቸው ከአገር ውስጥ ጋዜጠኞች ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ በመገናኘት፣ በአጠቃላይ የአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባለፈው ዓርብ ማለዳ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
“ጥያቄ ለማቅረብና ማብራሪያ በመሻት በመምጣታችሁ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡ ከዚሁ ቀጥሎ የምትፈልጉትን ጥያቄ እንደትጠይቁ ዕድል እሰጣለሁ፤” በሚል የመግቢያ ንግግር ጋዜጣዊ መግለጫውን የጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለሁለት ሰዓት ከ15 ደቂቃ የፈጀ ቆይታ ከጋዜጠኞች ጋር አድርገዋል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ የተገኙ ከ20 በላይ ጋዜጠኞች ያገኙትን ዕድል በመጠቀም በአገሪቱ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ በተለይም በቅርብ በተከሰተው የዓባይ ግድብ ውዝግብ፣ በሙስናና በሌሎች ጉዳዮች ላይ በርካታ ጥያቄዎችን በማቅረብ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ዝርዝር ምላሽ ሰምተዋል፡፡ በዋና ዋና አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት ማብራሪያ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ኢኮኖሚያዊና ተያያዥ ጉዳዮች
ከ2005 ዓ.ም. አጋማሽ በኋላ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ የአክሲዮን የንግድ ድርጅቶች ላይ የጣለው የዲቪደንድ ታክስ (የትርፍ ድርሻ ክፍፍል ላይ የሚጣል ታክስ) ጉዳይ በመጀመሪያ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበ ጥያቄ ነበር፡፡
የአገሪቱ የታክስ ሕግ የተጠቀሰውን የታክስ ዓይነት አስመልክቶ በተከፋፈለ የአክሲዮን ድርሻ ትርፍ ላይ የአሥር በመቶ ታክስ የሚጥል መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ በአክሲዮን የተቋቋሙ ድርጅቶች በአጠቃላይ የአሥር በመቶ ታክሱን የትርፍ ድርሻ ክፍፍል አደረጉም አላደረጉም በአጭር ጊዜ ሊከፍሉ ይገባል በሚል ባወጣው መመርያ፣ የንግዱ ኅብረተሰብን ሲያጉላላና ሲያከራክር ቆይቷል፡፡ ታክስ ባለሥልጣኑ ባወጣው መመርያ መሠረት ድርጅቶቹ የተጠቀሰውን ታክስ ወደኋላ ለአምስት ዓመታት በማስላት እንዲከፍሉ በመወሰኑ የተነሳ፣ ድርጅቶቹ በጉዳዩ ላይ ያነሱት የሕግ ጥያቄ ሳይመለስ ቅጣትን ፍራቻ ክፍያ እየፈጸሙ ይገኛሉ፡፡ የዚህን ታክስ አግባብነት የተጠየቁት አቶ ኃይለ ማርያም ተከታዩን ብለዋል፡፡
“ከትርፍ ድርሻ የሚከፈል ታክስ የሚጠየቀው የትርፍ ድርሻው ከተከፈለ ብቻ ነው፡፡ የትርፍ ድርሻው ሳይከፋፈል ለኢንቨስትመንት ከዋለ ታክስ አይከፈልበትም፡፡ ይህ የቆየ የመንግሥት አቋም ነው፤” ብለዋል፡፡
በታክስ ባለሥልጣኑና በንግዱ ኅብረተሰብ መካከል የተፈጠረው ክርክር የትርፍ ድርሻው ተመልሶ ለኢንቨስትመንት ውሏል? በሚል ጥያቄ ላይ መሆኑን አቶ ኃይለ ማርያም ከገለጹ በኋላ፣ መጣራት ያለበት የትርፍ ድርሻው ለባለሀብቶች ተከፋፍሏል ወይስ ለኢንቨስትመንት ውሏል የሚለው እንደሆነና ይህ እየተሠራ መሆኑን አሳውቀዋል፡፡
ስህተቱን የሠራው መንግሥት መሆኑ ከተረጋገጠ በንግዱ ኅብረተሰብ ላይ ለደረሰው መጉላላትና ጥቅም ማጣት መንግሥት ይቅርታ ይጠይቃል? የሚል ተያያዥ ጥያቄ ቀርቦላቸው፣ “ስህተት መኖሩን ካረጋገጥን ይቅርታ የማንጠይቅበት ምክንያት የለም፤” ብለዋል፡፡
ጉዳዩ አከራካሪ እንደሆነ በመጠቆምም አንዳንዱ ትርፉን ተቀብሎ መክፈል የማይፈልግ መኖሩን፣ ነገር ግን ለኢንቨስትመንት የዋለም እንደሚገኝ እንደሚገነዘቡና ይህንን ማጣራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ዕድገት ዙሪያ ከዚህ ቀደም ሲጠራጠሩ የነበሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ዕድገቱን ወደ መቀበል መምጣታቸውን፣ ነገር ግን እንደ የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ያሉ ተቋማት አሁንም የሚያወጧቸው መረጃዎች አሉ፡፡ ለአብነትም ዘንድሮ ይመዘገባል ብለው የገመቱት የኢትዮጵያ ዕድገትና የመንግሥት ግምት አሁንም የተለያዩ መሆናቸውን በተመለከተ፣ መንግሥትም ሌሎች ተቋማትም የሚግባቡበት በኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ኢንቨስትመንት መኖሩንና በዚህ መሀል የገንዘብ ፖሊሲውን በማጥበቅ የዋጋ ንረትን መዋጋት የሚለው የመንግሥት አቋም ግጭት የለበትም ወይ? እንዲሁም ባለፈው ዓመት የታየው የግብርና ምርት ዝቅተኝነት፣ በተመሳሳይም የኢንዱስትሪው ዘርፍ ዝቅተኛ አፈጻጸምን ከግምት በማስገባት ባለ ሁለት አኀዝ ዕድገት ዘንድሮ መጠበቅ አይከብድም ወይ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡
በሰጡት ምላሽም፣ “ላለፉት 11 ዓመታት በአይኤምኤፍና በኢትዮጵያ መንግሥት የዕድገት ትንበያ ዙሪያ ልዩነቶች ነበሩ፡፡ ወደ ትክክለኛው መረጃ ስንመጣ ግን የእኛን መረጃ ሲያስቀምጡ ነው የኖሩት፡፡ የለመድነው ነገር ዛሬ ቢደገም ምን አዲስ ነገር አለው፤” ብለዋል፡፡ በማከልም፣ “ግምት ግምት ነው ግምቱ ወደ እውነት መጠጋት ግን አለበት፤” በማለት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ግምት ሁሌም ወደ እውነት የተጠጋ እንደነበርና አሁንም እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
ባለፈው ዓመት 8.5 በመቶ ዕድገት እንዲመዘገብ ምክንያት የሆነው ግብርናው ያሳየው የ4.9 በመቶ ዝቅተኛ አፈጻጸም መሆኑን፣ በዚሁ ዓመት ተስተውሎ የነበረው የኢንዱስትሪ ዘርፍ ዝቅተኛ አፈጻጸም የመነጨው በጥቃቅንና አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገት ወደ 13 በመቶ በመውረዱ እንጂ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በ18.6 በመቶ አድጎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
የጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ያሳየው ዝቅተኛ አፈጻጸም አጠቃላይ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ወደኋላ እንደሳበው፣ ነገር ግን መንግሥት ካለፈው ዓመት ጀምሮ በጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ላይ በወሰደው ዕርምጃ ውጤት በመታየቱ፣ ከዚህ ባለፈም የግብርና ዘርፍ የሰብል ምርት ዕድገት ብቻ ስድስት በመቶ ማደጉንና ከስታስቲክስ ባለሥልጣን የተገኘው መረጃ ከሌሎቹ የግብርና የዘርፍ ዓይነቶች ዕድገት ጋር ሲደመር፣ ቢያንስ የግብርና ዕድገቱ ሰባት በመቶ ስለሚሆን ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የመንግሥት ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እያለ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር የሚለውን በተመለከተ ምላሽ የሰጡት፣ ከዋጋ ንረት ጋር በተያያዘ ሁለት ዓይነት አስተሳሰቦች መኖራቸውን በማስቀደም ነበር፡፡
“አንደኛው ዕድገት እያስመዘገቡ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር ሲሆን፣ ሁለተኛው ዕድገትን ገቶ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር ይገባል የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ ይህ ሁለተኛው አስተሳሰብ በምሥራቅ እስያ አገሮች ልምድ አልሠራም፡፡ ዕድገት እየመጣም የዋጋ ንረትን ተቆጣጥሮ መሄድ ይቻላል የሚለው በተግባር የተረጋገጠ ነው፡፡ በእኛም ሁኔታ ዕድገት እያስቀጠልን የዋጋ ንረትን ማውረድ ችለናል፤” ብለዋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት በሰጡት ማብራሪያ ዋናው ነገር የዋጋ ንረቱ ምንጭ እንደየአገሩ የሚለያይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ባደጉ አገሮች ያለው የዋጋ ንረት ምንጭና ግፊት ባላደጉ አገሮች ካለው ጋር ፈጽሞ እንደሚለያይ ተናግረዋል፡፡
“የእኛ መነሻ ምንድን ነው? የእኛ የምግብ ዋጋ ንረት ነው መነሻው፡፡ ዋናውና ትልቁ የግብርና ምርት ላይ ትንሽ ፈቅ ሲባል ዋጋው ይወርዳል፡፡ አርሶ አደሩ ዋጋ ወደቀ ብሎ መንጫጫት ይጀምራል፡፡ ስለዚህ መነሻው እንጂ አጠቃላይ ቲዎሪው አይደለም የሚወስነው፤” ብለዋል፡፡
ገንዘብ ወደ ኢኮኖሚው ውስጥ ሲገባ የሚያመጣው የዋጋ ግሽበትና በአቅርቦት ምክንያት የሚመጣውን ግሽበት መንግሥት ከፋፍሎ መመልከቱን አቶ ኃይለ ማርያም የገለጹ ሲሆን፣ “ገንዘብ በኢኮኖሚው ውስጥ በሚገባበት ወቅት ግሽበት አይፈጥርም ሳይሆን፣ አቅርቦት በሚጎልበት ወቅት የዋጋ ንረቱ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚጨምር አይተናል፡፡ ስለዚህ አቅርቦቱን በማሻሻል የዋጋ ንረቱን መቆጣጠር ይቻላል፤” በማለት አስረድተዋል፡፡
በማጠናከርም ግሽበትን ለመፍታት አቅርቦቱን ማሻሻል ማለት በሌላ በኩል ግብርናን ማሳደግ መሆኑንና ይህም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንደ መግደል እንሚቆጠር በመግለጽ ይህ ሊሆን የቻለው ከኢኮኖሚያዊ አወቃቀሩ የተነሳ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
የግብፅ ጉዳይ
በኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምክንያት የኢትዮጵያና በግብፅ መካከል ስለተከሰተው አለመግባባትና ችግሩን ለመቅረፍ ያለው ዕድል፣ የሁለቱ አገሮች አለመግባባትን ተከትሎ በግብፅ በኩል ስለታየው የጦርነት ጉሰማ አካሄድና የባለሙያዎች ቡድን ያቀረበውን ሪፖርት በተመለከተ ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት አስተያየት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ተፋሰሱን በጋራ የመጠቀም ፅኑ እምነትን አጉልተው አንፀባርቀዋል፡፡
“ፍላጎታችን በጋራ ብልፅግና ላይ የተመሠረተ ትብብር ይኑር የሚል ነው፡፡ ይህ አቋማችን ይቀጥላል፡፡ ይህንን አቋም የዓለም ኅብረተሰብ በአጠቃላይ እየተቀብለው ነው፤” ብለዋል፡፡
ሰጥቶ በመቀበል መደራደር ላይ የተመሠረተ አቋም በኢትዮጵያ በኩል መኖሩን በመግለጽ፣ የባለሙያዎቹ ቡድን ያቀረበው ሪፖርት ግድቡ የተፋሰሱን አገሮች ሊጠቅም እንደሚችል ያለማወላዳት እንዳስቀመጠ ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ የቡድኑ ሪፖርት ሌሎች የሰጣቸው የመፍትሔ ሐሳቦች መኖራቸውን ከዚህም ውስጥ የግድቡ ዲዛይንን እንደሚመለከት ገልጸዋል፡፡
ይህንንም ሲያብራሩ የግድቡ ኮንትራት የኢንጂነሪንግን ግዥና ግንባታን ያጠቃለለ መሆኑን፣ ይህም ማለት የመጀመሪያው ዲዛይን ብቻ ተሠርቶ ቀጣይ ዙር ዲዛይኖች በዚህ ላይ መሠረት ተደርገው እንደሚሠሩ፣ በመሆኑም ቀጣይ ዲዛይኖች ላይ መካተትና ሊተኮርባቸው የሚገባቸውን ሐሳቦች ባለሙያዎች በሪፖርታቸው እንዳቀረቡ ገልጸዋል፡፡
“የእኛ መንግሥት ከቀረቡት ሐሳቦች ውስጥ እጅግ አብዛኞቹን በአሁኑ የሥራ ወቅት በዲዛይኑ እያካተተ የሄደበት ሁኔታ አለ፡፡ ስለዚህ አስተያየቶቹን ለማካተት ቆም ብለን እንነጋገራለን የሚል ስምምነት ከግብፅ ጋር ተደርሷል፤” ብለዋል፡፡
ሌላው የባለሙያዎቹ ቡድን ግድቡ ሊፈጥር የሚችለው የአካባቢ ተፅዕኖ መጠናት ያለበት መሆኑን እንደጠቆመ የገለጹት አቶ ኃይለ ማርያም፣ “ግብፅና ሱዳን በዚህ ረገድ መረጃ ሊሰጡ ፈቃደኛ ስላልነበሩ ባለን መረጃ ላይ ብቻ ተመሥርተን ነው የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናቱን ያካሄድነው፤” በማለት በዚህ ጉዳይ ላይም ተነጋግሮ መሥራት እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ግብፅ ለመደራደር ዝግጁ መሆኗ ጥሩ ነገር እንደሆነ ነገር ግን ውጤቱን መተንበይ እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡ በድርድሩ ወቅትም ሆነ በማንኛውም ጊዜ ቢሆን፣ “የግድቡ ሥራ የማይቆም መሆኑንና መጠኑ የማይቀንስ መሆኑም መታወቅ አለበት፤” ሲሉም የመንግሥታቸውን አቋም ግልጽ አድርገዋል፡፡
የግብፅ ፕሬዚዳንት ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በግድቡ ዙሪያ በመወያየት በግልጽ በሚዲያ የታየው ኢትዮጵያን የማተራመስ አቋም ሆን ተብሎ ይሆን በስህተት ባይታወቅም፣ ከ120 ዓመታት በፊት ጀምሮ በግብፅ ይራመድ የነበረ አስተሳሰብ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
“በዚህ አስተሳሰብ መመራት ትክክል እንዳልሆነ ለግብፅ መሪ በተደጋጋሚ ገልጫለሁ፡፡ መንግሥታቸው ይህንን አቋም ይዟል የሚል እስካሁን አልሰማንም፤ ይህንን አቋም በያዘ ጊዜ ግን አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይገባሉ ማለት ነው፤” ብለዋል፡፡
የሙስና ጉዳይ
በቅርቡ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣናትና ባለሀብቶች በሙስና ተጠርጥረው መያዛቸውን ተንተርሶ፣ በኢሕአዴግ የፖለቲካ ልዩነት የተነሳ የተወሰደ ዕርምጃ ስለመሆኑና በቀጣይ የመንግሥት ተመሳሳይ ዕርምጃዎች ላይ ተጠይቀው በሰጡት ማብራሪያ፣ ዕርምጃው በኢሕአዴግ ጉባዔ እንዲሁም በማዕከላዊና በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ደረጃ ጥልቅ ውይይት ተካሄዶበት የተያዘ አቋም መሆኑን ገልጸዋል፡፡
“ኪራይ ሰብሳብነትን አንዳንዶች እስከሚያሾፉበት ድረስ እየተነገረ ያለ ቃል ነው፡፡ ይህንን ዕውን በማድረግ የድርጅታችን አንድነት፣ የመንግሥትና የሕዝብ ጠላት መታገል አለብን ብለን ነው ያስቀመጥነው፤” ሲሉ አክለዋል፡፡
የሙስና ሥራ የሰዶ ማሳደድ ሥራ ባለመሆኑ በተጠና መንገድ ሥራ መጀመሩን፣ በዋነኛ ደረጃ ከተለዩት ውስጥ የመሬት አስተዳደር ሥርዓቱ ላይ በተወሰደ ዕርምጃ ግለሰቦች ተጠያቂ እንደተደረጉ ገልጸዋል፡፡
ሙሰኞችን መቅጣት ብቻ ሙስናን መዋጋት አይደለም፡፡ ሥርዓቱ ለሙስና ምቹ እንዳይሆን ማድረግ ይገባል ከሚል ፅኑ እምነት በመነሳት የመሬት ሥርዓቱን የማስተካከሉ ሥራ መካሄዱን ተናግረዋል፡፡
“በሁለተኛ ደረጃ ታክስ ላይ መጥተናል፡፡ ቢሮክራሲውንም ከፍተኛ አመራሩንና ባለሀብቶችን ተጠያቂ አድርገናል፤” ብለዋል፡፡ “የፖለቲካ ልዩነት ስላለ ነው በሚል ለቀረበው ጥያቄ ይህንን ሊል የሚችል ካለ የፖለቲካ ልዩነት ሳይሆን የመቀራረብ ልዩነት ነው፡፡ ከሙሰኞች ጋር የተቀራረበ ካለ ደስ ሊለው ይችላል ብሎ መውሰድ አይቻልም፡፡ ….. ከየቤታቸው በሻንጣ የተከማቸ ገንዘብ እየወጣ እየታየ ምን የፖለቲካ ልዩነት ሊባል ይችላል?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ቀጣዩ መንግሥት ያተኮረበት የሙስና ምንጭ የመንግሥት ግዥ ዘርፍ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ኃይለ ማርያም፣ “ይህ አገር ከፍተኛ የመሠረተ ልማት እያካሄደ ነው፡፡ ከውጭ ባለሀብቶች ጋር ከፍተኛ የኮንትራት ስምምነትና ድርድሮች የሚደረግበት ነው፡፡ በመሆኑም የሙስና ምንጭ ነው፡፡ ስለዚህ በጥናት ላይ የተመሠረተ የመፍትሔ ዕርምጃ እንወስዳለን፤” ሲሉ ቀጣይ ዘመቻቸውን ጠቁመዋል፡፡

ከፌዴራል መንግሥት በጀት በሕግ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት ከተመደበው 20 ሚሊዮን ብር ውስጥ፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባት ሚሊዮን ብር ሕግን በመጣስ ኢሕአዴግ ለመረጣቸው ፓርቲዎች አከፋፍሏል በሚል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ ቀረበበት፡፡

ምርጫ ቦርድ ሕግ በመጣስ በኢሕአዴግ ለተመረጡ ፓርቲዎች ገንዘብ ሰጥቷል በሚል ጥያቄ ቀረበበት

ምርጫ ቦርድ ሕግ በመጣስ በኢሕአዴግ ለተመረጡ ፓርቲዎች ገንዘብ ሰጥቷል በሚል ጥያቄ ቀረበበ

“ፓርቲዎች ከዜጎች ገንዘብ እየተቀበሉ የቪዛ የድጋፍ ደብዳቤ ሲሰጡ ቦርዱ ችላ ብሏል” አቶ ግርማ ሰይፉ
“ሆደ ሰፊ የሆንነው ዴሞክራሲ እንዲጎለብት በማሰብ ነው” 
ፕሮፌሰር መርጋ በቃና
ከፌዴራል መንግሥት በጀት በሕግ በተቀመጡ መመዘኛዎች መሠረት ከተመደበው 20 ሚሊዮን ብር ውስጥ፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባት ሚሊዮን ብር ሕግን በመጣስ ኢሕአዴግ ለመረጣቸው ፓርቲዎች አከፋፍሏል በሚል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ ቀረበበት፡፡
በምርጫ ለሚሳተፉ ፓርቲዎች ሥራ ማስፈጸሚያና ለዕለት ተዕለት ተግባራት ማከናወኛ በጀት የማከፋፈል ሥልጣን የተሰጠው የምርጫ ቦርድ አመራሮች ለቀረበላቸው የሕግ ጥሰት ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጡ አልፈውታል፡፡ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የሥራ አመራሮች የ2005 ዓ.ም. አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ባለፈው ሐሙስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት፣ በተጠቀሰው የሕግ ጥሰትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠይቀዋል፡፡
የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና በዓመቱ ውስጥ የተካሄዱት የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤቶችና የአካባቢ ምርጫዎች ዴሞክራሲያዊና ነፃ ሆነው መጠናቀቃቸውን፣ ለዚህም ውጤት ቦርዱ ያከናወናቸውን ዝርዝር ተግባራት በ14 ገጽ ሪፖርታቸው ጨምቀው አቅርበዋል፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይም በክልል ምክር ቤቶች መቀመጫ ላላቸው አሥር የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዕለት ከዕለት ተግባር ማከናወኛ በጀት 20 ሚሊዮን ብር ከመንግሥት በማስፈቀድ ባላቸው መቀመጫ ብዛት ተሰልቶ የባንክ ሒሳብ ቁጥራቸውን ላሳወቁ ስምንት የፖለቲካ ፓርቲዎች ማከፋፈሉን የቦርዱ ሪፖርት ያስረዳል፡፡ ይሁን እንጂ ከተጠቀሰው 20 ሚሊዮን ብር የትኛው ፓርቲ ምን ያህል እንዳገኘ አልተካተተም፡፡
ሪፖርቱ ከቀረበ በኋላ በምክር ቤቱ ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ለፓርቲዎች የሚከፋፈል የመደበው 20 ሚሊዮን ብር በጀት ላይ ጠንከር ያለ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ከተጠቀሰው 20 ሚሊዮን ብር የትኛው ፓርቲ ምን ያህል ወሰደ የሚል ጥያቄ ማንሳት እንደማይፈልጉ፣ ምክንያቱ ደግሞ መመዘኛው በሕግ የተቀመጠና ቦርዱን የሚመለከት ባለመሆኑ እንደሆነ፣ ነገር ግን በመመዘኛው መሠረት ኢሕአዴግና አጋሮቹ አብዛኛውን እንደወሰዱት ግልጽ መሆኑን በመጠቆም ነበር አቶ ግርማ ወደ ጥያቄያቸው የገቡት፡፡
በመመዘኛው መሠረት ኢሕአዴግ ካገኘው ገንዘብ ውስጥ ሰባት ሚሊዮን ብር የሚሆነውን በራሱ ፍላጎት ለመረጣቸው ፓርቲዎች እንዲከፋፈልለት በመጠየቅ ለቦርዱ መመለሱንና ቦርዱም በኢሕአዴግ ለተጠቆሙት ፓርቲዎች ማከፋፈሉን አቶ ግርማ ገልጸዋል፡፡ ጥያቄያቸውም ያጠነጠነው በዚህ ላይ ነው፡፡
“የተጠቀሰው ሰባት ሚሊዮን ብር በሕግ መሠረት ለተፈለገው ዓላማ ነው ወይ የዋለው?” በሚል ጠንከር ያለ ድምፀት ጥያቄያቸውን ያነሱት አቶ ግርማ፣ “በመጀመሪያ ደረጃ በምክር ቤት ወንበር ለሌላቸው ፓርቲዎች የመንግሥትን ገንዘብ የማደል ሥልጣን ለኢሕአዴግ ማን ሰጠው?” በማለት አክለዋል፡፡ በመቀጠልም ገንዘቡን ኢሕአዴግ ሳይሆን ያደለው ምርጫ ቦርድ መሆኑ እንዳስገረማቸው፣ “ኢሕአዴግ እገሌ እገሌ ለሚባሉት ፓርቲዎች ስጡልኝ ብሎ በጠየቀው መሠረት ገንዘቡን ለተባሉት ፓርቲዎች ያደለው ምርጫ ቦርድ ነው፤” ብለዋል፡፡
ይህንኑ ጉዳይ በወቅቱ የቦርዱን ሰብሳቢ በአካል አግኝተዋቸው እንዴት ይህንን ታደርጋላችሁ የሚል ጥያቄ አንስተው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ግርማ፣ ሰብሳቢው ፕሮፌሰር መርጋ በቃና በወቅቱ ምን ክፋት አለው የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው በይፋ ተናግረዋል፡፡ “በእርግጥ በቅን ልቦና ስናስበው ምንም ክፋት የለውም፡፡ በሕግ ግን አይቻልም፡፡ በሕግ ላልተፈቀደላቸው ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድ ገንዘብ ማደል አልተፈቀደለትም፤” በማለት፣ “በየትኛው ሥልጣናችሁ ገንዘቡን እንዳደላችሁ ያስረዱን፤” ሲሉ ፕሮፌሰር በቃናን በምክር ቤቱ ፊት ጠይቀዋል፡፡
ባነሱት የሕግ ጥሰት ጉዳይ ላይ የበለጠ ማስረዳት የመረጡት አቶ ግርማ፣ “በምሳሌ ላስረዳዎት፤ መንገዶች ባለሥልጣን የተፈቀደለትን በጀት መጨረስ ስላልቻለ ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መስጠት አይችልም፤” ሲሉ የሕግ ጥሰቱን ለማሳየት ሞክረዋል፡፡
ከተጠቀሰው በመንግሥት ለፓርቲዎች የተፈቀደ 20 ሚሊዮን ብር በጀት ውስጥ ኢሕአዴግ በአከራካሪዎቹ መስፈርቶች ያገኘው ገንዘብ ግዙፍ ስለሆነበት ለሌሎች ፓርቲዎች እንዲከፋፈልለት ማድረግ እንደማይችል ገንዘቡን የማይፈልገው ከሆነ በሕግ አግባብ ማድረግ የሚችለው ለምርጫ ቦርድ መመለስ ብቻ ነው በማለት አስረድተዋል፡፡
“የእኔ ፓርቲ ከ20 ሚሊዮን ብር ውስጥ ለዓመት ሥራ ማስኬጃ የደረሰው ሦስት ሺሕ ብር ነው፡፡ እኛ ስለማይበቃን ገንዘቡን እንደመለስነው ኢሕአዴግም ይህንን ነበር ማድረግ ያለበት፤” ብለዋል፡፡ በማከልም ይህ ስህተት ሊታረም ይገባል ብለው፣ የሚታረመው ሌሎች ምክንያቶችን በመደርደር ሳይሆን ኢሕአዴግ ከሌላ የገንዘብ ምንጩ የተከፋፈለውን ገንዘብ ለምርጫ ቦርድ በመመለስ ብቻ ነው በማለት ተከራክረዋል፡፡
ከዚህ በተለየ ጉዳይ ጥያቄያቸውን ለምርጫ ቦርድ አመራሮች ማቅረባቸውን በመቀጠል፣ የመደራጀት መብት በአገሪቱ ስላለ ብቻ የፖለቲካ ፓርቲ እየመሠረቱ ነገር ግን ለፖለቲካ ተልዕኮ ሳይሆን ለሕገወጥ የገንዘብ መሰብሰቢያነት የሚጠቀሙ ፓርቲዎች መኖራቸው በግልጽ እየታወቀ፣ ቦርዱ ቸልተኝነትን መርጧል በማለት፣ “ሥራችሁ ምንድን ነው? ምንድን ነው የምታደርጉት?” ሲሉ አቶ ግርማ ጠይቀዋል፡፡ “በአሁኑ ወቅት ንግድ ፈቃድ ከማውጣት የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃድ ማውጣት ይቀላል የተባለው እውነት እየሆነ ነው፡፡ ነገር ግን ንግድ ፈቃድ ያወጡ ግለሰቦች ፈቃዱን ካልተጠቀሙበት ይሰረዛሉ፤” የሚሉት አቶ ግርማ፣ “ፓርቲዎች ምን ሲያደርጉ ነው እዚህ አገር የሚሰረዙት?” በማለት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ለዚህ ጥያቄያቸው ራሳቸው የሰጡት ምላሽ፣ የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃድ ያላቸው ድርጅቶች ከፖለቲካ ዓላማ ይልቅ ከዜጎች ገንዘብ እየተቀበሉ የውጭ አገር የቪዛ ማስመቻ ድጋፍ ደብዳቤ በመጻፍ ዜጎችን ለስደት እየዳረጉ ነው የሚል ነው፡፡ “መንግሥት ለፓርቲዎች የሰጠውን የመንግሥት ቤት ለሌላ ሦስተኛ ወገን አከራይተው በጥቅም ሲጣሉ በሚዲያ እየተሰማ ቦርዱ ግን ዝምታን መርጧል፤” ሲሉ ተጨማሪ ወቀሳ ሰንዝረዋል፡፡
ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት የጀመሩት ፕሮፌሰር መርጋ በቃና፣ ለፓርቲዎች ተብሎ ከመንግሥት የሚመደበውን የድጎማ ገንዘብ ቦርዱ የሚያከፋፍለው ሕግን መሠረት አድርጎ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በሕጉ መሠረትም ፓርቲዎቹ በፌዴራልም ሆነ በክልል ምክር ቤቶች ውስጥ ያላቸው መቀመጫ ብዛት አንደኛው መስፈርት መሆኑን፣ የሌሎቹ ፓርቲዎች ለቅስቀሳ ዘመቻ የሚያስፈልጋቸውን ወጪ በገንዘብና በዓይነት የሚሸፈን እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
በዚህ መስፈርት መሠረት ተጠቃሚ መሆን የሚገባቸው አሥር ፓርቲዎች እንደነበሩ፣ ከእነዚህ ውስጥ ለስምንቱ መከፋፈሉን ሁለቱ ግን የገንዘቡ መጠን ስላነሰባቸው አለመቀበላቸውን ገልጸው፣ “ገንዘቡን የወሰዱ ፓርቲዎች በምን ላይ እንዳዋሉት ኦዲት አስደርገው ማቅረብ አለባቸው፤” ብለዋል፡፡ ከዚህ ባለፈ ቦርዱ በኢሕአዴግ ጠቋሚነት በሕጉ መሠረት ለማይገባቸው ፓርቲዎች አከፋፍሏል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም፡፡
ፓርቲዎች ሕግን እንዲያከብሩ በተደጋጋሚ እየመከሩ መሆኑን የሚገልጹት ፕሮፌሰር መርጋ፣ “ሕጉ ሙሉ ለሙሉ ቢከበር ለቦርዱም ሥራ ቀለለለት ማለት ነው፡፡ ነገር ግን በሆደ ሰፊነት ነው የምንሠራው፡፡ ምክንያቱም ለዴሞክራሲና ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓት መጎልበት ሲባል፤” ብለዋል፡፡
ቦርዱ በዚሁ ሁኔታ ይቀጥላል ማለት እንዳልሆነ የጠቆሙት ሰብሳቢው ሕግን ማክበር በማይችሉ ላይ ዕርምጃ ይወስዳል ብለዋል፡፡ “ለምሳሌ አራት ፓርቲዎች ፈቃድ ከወሰዱ በኋላ ከቦርዱ ጋር ግንኙነት በማቋረጣቸውና በተደጋጋሚ በሚዲያ ጥሪ ቢተላለፍላቸውም ባለመገኘታቸው ተሰርዘዋል፤” የሚሉት ፕሮፌሰር መርጋ፣ በአሁኑ ወቅት ፈቃድ ካላቸው 76 ፓርቲዎች ውስጥ 22 የሚሆኑት ሕጉን ሙሉ ለሙሉ ያሟሉ መሆናቸውን፣ የተቀሩት ግን በከፊል ማሟላታቸውንና ከእነዚህ ጋር በቀጣይ ሕግ የማስከበር ሥራን በመወያየት እንደሚያከናውኑ አብራርተዋል፡፡

የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ከአገር እንዳይወጡ ታገዱ

6dfc868ecccfc66f6592d0a6b7e266ba_XL

30 June 2013
ፍርድ ቤት ቀርበው በ25 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቁ
የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ፣ ተጠርጥረው በተከሰሱበት ከፍተኛ የማታለል ወንጀል ምክንያት ከአገር እንዳይወጡ ሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. የእግድ ትዕዛዝ ተላለፈባቸው፡፡
ቀደም ባለው ቀጠሮ ሳይቀርቡ በመቅረታቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አምስተኛ ወንጀል ችሎት ለሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. ታስረው እንዲቀርቡ ባዘዘው መሠረት ሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. የቀረቡ ሲሆን፣ በመጀመርያ ቀጠሮ ያልቀረቡበት ምክንያታቸውን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡
በሕመም ምክንያት ሊቀርቡ አለመቻላቸውንና በዕለቱም በሕመም ላይ መሆናቸውን ለችሎቱ አስረድተዋል፡፡ ሰኔ 11 ቀን 2005 ዓ.ም. ተጠርጣሪዎቹ የተመሠረተባቸው ክስ ተሰምቶ የእምነት ክህደት ቃላቸውን መስጠት ቢገባቸውም፣ ዓቃቤ ሕግ ከክሱ ጋር የሚያያይዘው ቀሪ ማስረጃ እንዳለው ገልጾ፣ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጠው በመጠየቁ ክሱ ሳይሰማ ቀርቷል፡፡
ሌላው ዓቃቤ ሕግ ለችሎቱ ያመለከተው ጉዳይ ተጠርጣሪዎቹ በአርበኞች ማኅበር ሠራተኞች ላይ ዛቻና ማስፈራራት እያደረሱ መሆኑን፣ ፕሬዚዳንቱ ቢሮ ባይገቡም ቤታቸው ውስጥ ሆነው እየሠሩ መሆናቸውን፣ በዚህ ሁኔታ ከቀጠሉ የማኅበሩ ንብረቶች አደጋ ላይ መሆናቸውን በማስረዳት፣ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥለት ጠይቋል፡፡
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆችም ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ማመልከቻ በማስረጃ የተደገፈ መሆኑን ለችሎቱ በመግለጽ፣ የዓቃቤ ሕግ አቤቱታ ተዓማኒነት እንደሚጐድለው በማስረዳት አቤቱታው ውድቅ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል፡፡ ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄም በቤታቸው መሥራታቸው ለመታመማቸው ማስረጃ እንደሆነም አመልክተዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ድብደባ፣ ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰባቸው ስላሉት የማኅበሩ ሠራተኞችና የዓቃቤ ሕግ ምስክሮችን በሚመለከት ዓቃቤ ሕግ በማስረጃ የተደገፈ አቤቱታ በጽሕፈት ቤት በኩል እንዲያቀርብ በማሳሰብ፣ ፕሬዚዳንቱ በ25 ሺሕ ብር ዋስ እንዲለቀቁ አዟል፡፡ ክስ ለመስማትና የእምነት ክህደት ቃል ለመቀበል ለሐምሌ 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Saturday, June 29, 2013

ተመስገን ደሳለኝ ለማን ደስ ይበለው ብሎ ጠፋ!? (ከአቤ ቶኪቻው)

394711_184013551696255_1365830121_n
ተመስገን ደሳለኝ ለማን ደስ ይበለው ብሎ ጠፋ!?
ባለፈው ጊዜ አንድ ወዳጄ ጋር አዲሳባ ስልክ ደውዬ ሳናግረው በአካባቢው ከእርሱ ድምጽ ጎልቶ የሚሰማ የመኪና ጥሩንባ ሰማሁና ይሄ ሁሉ የመኪና ጥሩምባ ምንድነው… ብዬ ጠየኩት፡፡
ሃይለማሪያም ደሳለኝ እየገቡ ወይም እየወጡ ነው መሰለኝ መንገድ ተዘጋግቷል፡፡ አለኝ፡፡
ወዲያውም ቀጠል አድርጎ፤ እንደ ሀቁ ቢሆን ኖሮ መንገድ መዘጋጋት የነበረበት ለሀይለማሪያም ደሳለኝ ሳይሆን ለተመስገን ደሳለኝ ነበር… አለኝና በቁጭት፤ ይሄው የሚያጅቡትን አያቀውቁምና… እልኩ እያታዘብኩ ነው…! ሲል አወጋኝ!
ተመስገን ደሳለኝ ገዢውም ተገዢውም ፓርቲ ሊያመሰግነው የሚገባ ጋዜጠኛ ነው፡፡ ነገር ግን ገዢዎቻችን ማመስገን የሚቆጥር ይመስል ሰውን ማመስገን አይወዱም፡፡ ስለዚህ ተሜንም በማመስገን ፈንታ ከሰሱት፡፡ ጎሽ በማለት ፈንታ እንደ ጎሽ ሊወጉት ቀንዳቸውን አሾሉበት፡፡ እሰይ በማለት ምትክ ሰይ ባንከረባብት ብለው ለሁለቱም አሰቡት፡፡ (ለማሰርም ለማሰደድም) (ሰይ ባንከረባብት በልጅነታችን ብይ ጨዋታ ላይ ተወርዋሪዋ ብይ ጉድጓዳ ውስጥ ብትገባም የተቃራኒውን ብይ ብትመታም ነጥቡ እንዲያዝልን ውል የምንገባባት ቃል ነበረች፡፡)
ተመስገን ደሳለኝ እንዲሰደድ መንግስት ከፀሎት ጀምሮ ሁሉንም አይነት የትግል ስልቶችን እንደተጠቀመበት ትዝ ይለኛል፡፡ ለምሳሌ ባለፈው ጊዜ ምንም የቀጠሮ ወረቀት ወይም መጥሪያ ሳይሰጠው በራዲዮን፤ “ተመስገን ደሳለኝ በሌለበት የፍርድ ሂደቱ ታየ ለሚቀጥለው ጊዜ ፖሊስ ይዞ እንዲያቀርበው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል!” የሚል አይነት ዜና በሰላም ቁጭ ብሎ ሻይ በሚጠጣበት ካፌ ውስጥ ሰማ፤ (እናጋን ካልን ደግሞ ዜናውን እንደውም ያነበቡት ተሜ ልክ ዜና ሲሰማ አይተው ነው…! ማለት እንችላለን…) የዚህ ዜና አላማ ግልፅ ነበር፡፡ ተሜ ደንግጦ ፖሊስ ሳይዘው በፊት መንገዱን እንዲያያዘው ማድረግ ነበር፡፡ ወዳጃችን ግን፤ ብታስሩኝ ባለ ጊዜም ባለ ብረትም ናችሁና እግሬ እምቢ ማለት አይቻለውም፡፡ ለመሰደድ ግን እሺ የሚል እግር የለኝም፡፡ ብሎ እንቅጩን ነገራቸው እና የመጣው ምጣ ብሎ ቁጭ አለ…
በነገራችን ላይ ተመስገን እስከ አሁን ድረስ በመንግስት የተሰነዘረበት ክስ ስፍር ቁጥር የለውም፡፡ እንደው የሪከርድ መዝጋቢ መስሪያ ቤቶች የሚያስታውሳቸው አጥተው እንጂ ከዚህ ሁሉ ክስ ጋር አብሮ መኖር የቻለ ጋዜጠኛ ብለው ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ የሚያሰፍሩት ሁሉ ይመስለኛል፡፡ መንግስታችን በክስ ላይ ክስ ሲደራርብ ሲደራርብ ክሱ ተቆልሎ አለመናዱም የእግዜር ተዓምር ነው፡፡ አንዱ ሳይቋጭ አንዱን አንዱ ሳይቋጭ አንዱ ክስ ሲመጣ በአሁኑ ሰዓት ተመስገን ደሳለኝ ከሃምሳ በላይ ክሶች ጋር ተመስገን ብሎ እየኖረ ነው፡፡
የተሜ እና የእኛ ፍትህ ጋዜጣ “መለስ ሞቱ” በማለቷ እኛ ሳንል ምን ሲደረግ እንዲህ ትያለሽ ተብላ ከሳላሳ ሺህ ኮፒ በላይ እንድትቃጠል ተደረገች፡፡ (የመለስ አምልኮ ይሎዎታል ተመስገን…!) አንዱ ሲዘጋ በአንዱ እንከሰታለን በምትለው ስትራቴጂ መሰረት፤ አዲስ ታይምስ ተተካች፡፡ አዲስ ታይምስ ደግሞ “ብር ከየት አምጥታችሁ ነው…” ተብላ ህትመቷ ተከለከለ፡፡ መንግስታችን እንደሆነ ኮሚክ ነው ጮክ ብለን በያይነቱ ስናዝ ራሱ “ብር ከየት አምጥተው ነው” ብሎ ይጨንቀዋል፡፡ በእርሱ ቤት እርሱ አበል ያልሰጠው ሰው፤ ወይም ከአዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም ያልተበደረ ሰው ምንም ገንዘብ የለውም…!
ተመስገን እና ጓደኞቹ እጅ መስጠት ብሎ ነገር አያውቁም ነበር፤ እና ከየትም ከየትም ብለው ድጋሚ ልዕልና ጋዜጣን አበረከቱልን፡፡ መንግስት መንግስት ሆኖ እንጂ… በብስጭት ካቲካላ ይጠጣ ነበር፡፡ ግን ሳይጠጣም ሞቅ አለው፡፡ ሰከረም፡፡ እናም ልዕልናንም ጥርቅም አድርጎ ዘጋት፡፡ (ይህ ውሳኔ የሞቅታ ካልሆነ ሌላ ሊሆን አይችልም)
ተመስገን ደሳለኝ ሲናገር ሰዎቻችን ደስ አይላቸውም፡፡ እናም በተቻለ አቅም ዝም ማሰኘት ይፈልጋሉ፡፡ ልጁ ግን በቀላሉ ዝም ብሎ የሚያስደስታቸው አልነበረም፤ በማህበራዊ ድረገፆች የሚተነፍሰውን ይተነፍስ ጀመር፡፡
ኢህአዴግ ሰው እንደማትንቅ ያወኩት እኔ ምስኪኑን ሳይቀር ለመከታተል የደህንነት ሰው የመደበች ዕለት ነው፡፡ ለተመስገን ደሳለኝማ ሁሉን አቀፍ የትግል ስልት ነው የተጠቀመችበት፡፡ በእውነቱ ከሆነ፤ ለአንድ ግለሰብ ሁሉን አቀፍ የትግል ስልት መጠቀም ትልቅ የሀይል ብክነት ነው፡፡ ፍጹም ተመጣጣኝ ያልሆነ ርምጃ፤ ጎጆ ቤትን በሚሳኤል እንደ መደብደብ በሉት…
ተሜ በኢህአዴግ ክሶች ብዛት፤ በኢህአዴግ ሚዲያዎች ማስፈራራት፣ በኢህአዴግ የደህንነት ሰዎች ከበባ፣ በኢህአዴግ ማተሚያ ቤቶች አድማ አበሳውን አየ፡፡
“አንበሳው” መንግስታችን ተመስገን ግለሰብ ነው ብሎ አልናቀውም፡፡ ያለውን አቅም ሁሉ ተጠቅሞ ሊገድበው ተንቀሳቅሷል፡፡ እርሱን ለመገደብ ያላደረገው ነገር ቢኖር ቦንድ ግዙ ብቻ አላለንም፡፡ ለአባይ የምንገዛው ቦንድ ብዙ ነገር ይገድባልና!
አሁን ተመስገን ደሳለኝ ከሜዳው ላይ ጠፍቷል፡፡ ከመንግስታችን ሃይል የተሞላበት አጨዋወት አንጻር እስከዛሬም በቃሬዛ አለመውጣቱ የሚገርም ነበር፡፡ ነገር ግን ያንን ሁሉ ችሎ ሜዳው ላይ ስናየው እኛ ደስ ይለን ነበር፡፡ አሁን ታድያ ሲጠፋብን ጊዜ በአዲስ መስመር ላይ ጮክ ብለን እንጮሃለን እንጂ እንደምን ዝም እንላለን…
ተመስገን ደሳለኝ ሆይ ማን ደስ ይበለው ብለህ ጠፋህ…!

ኢትዮጵያዊቷ አሰሪዋን ገላለች ተብላ በስቅላት ተቀጣች

Ethiopian Maid Sentenced to Death by Hanging for Decapitating Sponsor
by Arba_Gorash » Today, 15:08
Ethiopian Maid gets death for decapitating sponsor
KUWAIT CITY, June 27: The Criminal Court presided over by Judge Adnan Al-Jasser has sentenced an Ethiopian woman to death by hanging for murdering her sponsor the day before the latter’s wedding.
According to the case files, the Ethiopian housemaid beheaded her 25-year old sponsor in the family house in Jaber Al-Ali area a day before the victim’s wedding and ran away.
However, officers from Criminal Investigation Department managed to apprehend the suspect at Kuwait International Airport before she took a flight to escape from the country.
During interrogations, the suspect confessed that she had first stabbed the victim while she was asleep. When the victim woke up, the suspect slashed her neck using a cleaver until her head fell off from the body

በከፍተኛ ሙስና የተዘፈቀው መከላከያ ሂሳቡ እንዳይመረመር ታዘዘ



ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና :-የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በሚያዚያ ወር 2005 ዓ.ም ባቀረበው ሪፖርት የመከላከያና የደህንነት ተቋማት
የፋይናንስ አያያዝ ከፍተኛ ችግር እንዳለበት ማመልከቱን ተከትሎ በየመ/ቤቶቹ የተነሳውን ቅሬታ ለመፍታት በቀጥታ
እነዚህን ተቋማት በተለየ ሁኔታ ኦዲት ለማድረግ የሚያስችል አዋጅ እየተረቀቀ መሆኑ ተጠቆመ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር አቶ ገመቹ ዱቢሶ ሚያዚያ 22 ቀን 2005 ዓ.ም ለፓርላማው ባቀረቡት የ2004 ዓ.ም
የፌዴራል የመንግስት መ/ቤቶች የሂሳብ አያያዝ ሪፖርት በተለይ በዘጠኝ መ/ቤቶች 3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር
ባልተሟላ ሰነድ ወጪ ሆኖ መገኘቱን፤ ከዚህ ውስጥ 3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብሩ የመከላከያ ሚኒስቴር መሆኑን
መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
እነዚህ ተቋማት ላወጡት ገንዘብ ትክክለኛ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ተጠይቀውም ማቅረብ አለመቻላቸውን ለፓርላማው
ሪፖርት ካደረጉ በኋላ በተለይ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈረጌሳን ጨምሮ የተለያዩ ሹማምንት ሪፖርቱን
በአደባባይ እስከማብጠልጠል የደረሰ ትችት ሲያቀርቡ ተደምጠዋል፡፡ ዋናው መከራከሪያቸውም የመከላከያ ወጪ ሚስጢር
ነው የሚል ነበር፡፡
ይህንን ተከትሎ የፓርላማ አፈጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ በቴሌቪዥን ቀርበው “ባልተሟላ ሰነድ
ወጪ ተደረገ ማለት ብሩ ተበላ ማለት አይደለም” በማለት ማብራሪያ ለመስጠትና ተቋሙን ከተጠያቂነት ነጻ ለማድረግ
ሞክረዋል፡፡
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከተሾሙ በኋላ የመጀመሪያቸው የሆነውን መግለጫ ትላንት ጠዋት
በጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጡበት ወቅት በተመሳሳይ መንገድ መከላከያን ኦዲት ማድረግ
ሚስጢር ማባከን መሆኑን በመግለጽ በቀጣይ ሁኔታውን ለማስተካከል አዲስ ሕግ እንደሚወጣ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡
ዋና ኦዲተር በአዋጅ ቁጥር 669/2002 መሰረት የፌዴራል የመንግስት ተቋማትን ኦዲት የማድረግና የማስደረግ ሙሉ ሥልጣን እንደተሰጠው ጠቅላይ ሚኒሰትሩ አስታውሰው በዚህ ሕግ መሰረት ባለፉት ዓመታትም መከላከያን ጨምሮ ሁሉንም ተቋማት ኦዲት ሲያደርግ መቆየቱን አስረድተዋል፡፡
አቶ መለስ ዜናዊ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ በሚያዚያ ወር 2004 ዓ.ም የ2003 የሂሳብ ሪፖርት ለፓርላማው ቀርቦ እንደነበር በዚህም ሪፖርት መሰረት ከተወቀሱት ተቋማት መካከል መከላከያ አንዱ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ በ2003 በጀት ዓመት በመከላከያ 133 ነጥብ
8 ሚሊየን ብር ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ መኖሩን፣ የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 19 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በወጪ
ተመዝግቦ መገኘቱን ሪፖርት አድርጓል፡፡  በተጨማሪም የወጪውን ትክክለኛነት ማረጋገጥ ካልተቻለው ገንዘብ መካከል 1
ነጥብ 9 ቢሊየን ብር የመከላከያ ሲሆን ፣ 54 ነጥብ 3 ሚሊየን ደግሞ ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ 33
ነጥብ 34 ሚሊየን ብር የአገር ውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ መሆኑ መጠቀሱ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ መ/ቤቱ
እንደዘንድሮ ከፍተኛ ቅሬታ ያላቀረበ ሲሆን የዘንድሮ ቅሬታ ምናልባትም በአዲሱ ጠ/ሚኒስትር ላይ ተጽዕኖ በማሳደር
ነገሩን ለመሸፋፈን የታሰበ ሳይሆን እንደማይቀር ተገምቷል፡፡
ምንጮቻችን እንደገለጹት በአገሪቱ ከፍተኛ ሙስና ከሚፈጸምባቸው ተቋማት መካከል ግንባር ቀደሙ መከላከያ መሆኑን
አስታውሰው አንድ ወርሃዊ ደመወዙ 4 ሺ ብር የማይሞላ ከፍተኛ የመከላከያ ሹም በአዲስአበባ ቁልፍ ቦታዎች ጭምር
በሚሊየን ብር የሚገመቱ ቪላዎችንና ሕንጻዎችን የሚገነባበት እንዲሁም ትልልቅ ንግዶችን የሚያንቀሳቅስበት ሁኔታ
የአደባባይ ሚስጢር ነው በማለት የእነአቶ ኃይለማርያም ሙግት ጥቅሙ ለሙሰኞቹ ነው ብለዋል፡፡
አዲሱ ሕግ በቀጣይ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ዋና ኦዲተር ሕጉ እስኪጸድቅ
መከላከያና የደህንነት ተቋማትን ኦዲት እንዳያደርግ መታዘዙንም ምንጮቻችን አረጋግጠዋል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ 60 ከፍተኛ ጀኔራሎች መካከል 58ቱ በትጥቅ ትግሉ ወቅት የህወሀት አባል ሆነው የመጡ ናቸው።  መከላከያን ከላይ ሆነው የሚዘወሩት 7ቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በሙሉ የህወሀት ታጋዮች ናቸው። ባለፉት 22 አመታት በዚህ ከፍተኛ አመራር ውስጥ የሌላ ብሄር ተወላጅ ተካቶ አያውቅም።
በሌላ በኩል ደግሞ አቶ ሀይለማርያም በአባይ ግድብ ዙሪያ ከተቃዋሚዎች ጋር እንደማይነጋገሩ አስታውቀዋል።

ሰበር ዜናበጎንደር ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አባላት መታሰራቸው ቁጣን ቀሰቀሰ

 

-አንድነት በየትኛውም የመንግስት ህገወጥ ጫና ሰልፉን እንደማይሰርዝ ይፋ አድርጓል
በጎንደር ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 4 የአንድነት አባላት በፖሊስ መታሰራቸው በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ቁጣን ቀሰቀሰ፡፡ አንድነት ምንም አይነት ህገወጥ እስር በጎንደር የተዘጋጀውን የተቃውሞ ሰልፍ እንደማያስቆመው አሳውቋል፡፡
ዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2005 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ምዕራብ አርማጨሆ በጎንደር  ሰኔ 30 የሚደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ የሚመለከት በራሪ ወረቀት በማሰራጨት ላይ የነበሩት አለልኝ አቧይ፣ ዋኘው፣አብርሀም ልጅ አለም፣አንጋው ተገኝ የተባሉት የአንድነት አባላት ህገወጥ በሆነ መንገድ በአካባቢው ፖሊሶች መታሰራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችን እንዳስቆጣ ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመላክቷል፡፡ ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ወረቀት በመበተናቸው ብቻ የታሰሩት ግለሰቦች ሁኔታ የስርአቱን አምባገነንነት አመላካች ነው፡፡
የዞኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች “እስር ለጎንደር ነዋሪ በተለይም ለአንድነት አባላት አዲስ አይደለም” ካሉ በኋላ “የታሰሩት አባሎቻችንን ለማስፈታት ከምናደርገው ጥረት ጎን ለጎን የቅስቀሳ ስራው እንዳይስተጓጎል ተጨማሪ አባላት የቅስቀሳ ስራውን እንዲቀጥሉ ወደ ስፍራው ልከናል፡፡” ብለዋል፡፡
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ሙላት ጣሰው ለሰሜን ጎንደር አስተዳዳሪ ለአቶ ግዛቴ አብዩ ስልክ በመደወል የታሰሩት የአንድነት አባላት በአፋጣኝ መፈታት እንዳለባቸው ተናግረው ገዢው ፓርቲ የሚያደርገው አፈና ከህዝባዊ ንቅናቄ እንቅስቃሴያችን አያስቆመንም በማለት አሳስበዋል፡፡
አንድነት ፓርቲ የሚጠበቅበትን ስለሰልፉ የማሳወቅ ተግባር አጠናቆ ቅስቀሳ የጀመረ ቢሆንም በበጎንደር ምዕራብ አርማጨሆ የተቃውሞ ሰልፉን አላማ የሚያብራራ በራሪ ወረቀት በማሰራጨት ላይ የነበሩ አባላቱ በህገወጥ መንገድ ከመታሰራቸውም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች የአንድነት ፓርቲ የቅስቀሳ ቡድን አባላት የሚደርስባቸውን ማስፈራሪያ ወደ ጎን ብለው ቅስቀሳውን አጠናክረው መቀጠላቸውንና የአከባቢው ነዋሪም በራሱ ተነሳሽነት በራሪ ወረቀቶችንና መረጃዎችን በማስተላለፍ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝ የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ጎንደር ዞን አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት አስታውቀዋል፡፡
አንድነት ፓርቲ በጎንደር ለሚደረገው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ የጎንደር ከተማና አከባቢው ነዋሪዎች በስፋት እንዲሳተፉ በቀየሰው ስትራቴጂ መሰረት ስኬታማ ቅስቀሳ እያደረገ ሲሆን ሁለተኛው የቅስቀሳ ቡድንም ዛሬ ወደ ጎንገር መንቀሳቀሱ ታውቋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚጠይቀዉ አንድ ጥያቄ ነዉ።

እንደሚታወቀው በአንድ ሃገር የኤኮኖሚ፣ የፖለቲካና የማህበራዊ ክንውኖች የቀን ተቀን ለውጥ ውስጥ የህብረተሰብ ተሳትፎ(አስተዋጾ) ጉልህ ሚና አለው፡፡ እንዲሁም በሂደትቱ ውስጥ የሚያጋጥሙ አገራዊ ጠቀሜታ ያላቸው ጉዳዮችም ይሁኑ ወይም በተቃራኒው የሚከሰት ተፈጥሯዊም ሆነ በመልካም አስተዳድር ችግር ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮች ከህብረተሰብ ጫንቃ ላይ አይወርድም፡፡ ይህ ስለሚታወቅ ሃላፊነት የሚሰማቸው፣ ለሃገርና ለሕዝብ ታማኝ የሆኑ፣ በሕዝብ ይሁንታ ስልጣን የያዙ መንግስታት ያላቸው ሃገሮች በየትኛውም ሃገራዊ እንቅስቃሴ ላይ ሕዝባቸውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተሳታፊ በማድረግ በብሔራዊ ስሜት የታነፀ በሃገሩ ጉዳይ የማያመነታ ህብረተሰብ ይገነባሉ፡፡ የእንደኛ አይነቶቹ የሃገርና የሕዝብ ፍቅር የሌላቸው አምባገነን መሪዎች ግን እንኳን የሃገርህ ጉዳይ ያገባሀል ብለው ሊያሳትፉት ቀርቶ የሕዝብን የመናገርና ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ ተፈጥሮዊ መብቱን ገፈው ሃገሪቱን የቁም እስር ቤት አርገዋታል፡፡Image

ነፃነት፣አንድነት፣ፍትህ እና እኩልነት በወሬና በዲስኩር አይመጣም:: የመስዋዕቱ አይነት ይለያይ እንጂ አነሰም በዛም የነፃነት ትግል ወይ ሃብትን ወይም የህይወት መስዋዕትነት ይፈልጋል፡፡ ዶክተር ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁንየር እንዳለው “ለውጥ በመንኮራኩር ተጭኖ የሚቀርብ ነገር አይደለም ፣ በማያቋርጥ ትግል እንጂ ፣ ወገባችንን ጠበቅ አድርገን ለነፃነታችን መጣር አለብን ”፥ ይህ ነው እውነቱ:: ይህንን ሁሉ በህዝብና በሃገር ላይ የሚደርሰውን ለከት ያጣ ጭቆና የምናይ እና የምንሰማ በተለይ በሰለጠነው አለም የምንኖር ወገኖች እኛ በሰው ሃገር የምናገኘውን የመናገር ፣የመሰብሰብ እና የመፃፍ ነፃነት ወገናችን በገዛ ሃገሩ ሲያጣ፣ ይህ ነው የማይባል ችግር ሲወርድበት ከወሬ ያለፈ በተግባር መልካም ውጤት የሚያመጣ ስራ ለመስራት ቆርጠን ልንነሳ ይገባል:: የህይወት መሰዋዕትነት ለሚከፈልበት የነፃነት ትግል ቢያንስ በገንዘብ በማገዝ አጋርነታችንን ማሳየት አለብን:: የወያኔን ተንኮል ችላ ካልን የወገኖቻችንን የመከራ ጊዜ እናራዝማለን ማለት ነው:: ቁጥር ስፍር የሌለው ህዝብ በውጪው አለም እየኖረ ስለምን የህዝባችን የመረጃ ምንጭ የሆኑትን ነፃ ሚድያዎች መስራት ያለባቸውን ያህል እንዲሰሩና ህዝባችን እየተራበ መጥገቡን፣ እየከሰረ ማትረፉን፣ እየተቸገረ መበልፀጉን ከሚነገረው የወያኔ ዲስኩር አውጥተን አማራጭና እውነተኛ መረጃ የሚያገኝበትን፣ ወያኔ የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም በከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲው እያደረገ ያለውን ዘርን ከዘር ሃይማኖት ከሃይማኖት የማጋጨትና የመሳሰሉትን የወያኔን ሴራ ህዝቡ እንዲያውቅና በአንድነት ለመብቱና ለነፃነቱ እንዲነሳ በማድረግ የዜግነት ግዴታችንን መወጣት አለብን፡፡
የወያኔ ጁንታ 11% እድገት አሳይተናል እያለ በሌለ ተስፋ ላይ ተቀምጦ በሚኮፈስበት እና ሳተላይት አመጠቅን፣ አይሮፕላን ሰራን፥ እያለ ትምክህቱን በሚያሳይበት በአሁን ወቅን በሃገራችን መኖር ያልቻልን ኢትዮጵያውያን ድንበር አቋርጠን በተፈጥሮ የበለጸገች ሀገራችንን ጥለን ወደ ተለያዩ ሀገራት በስደት ተበትነን እንገኛለን:: የዘረኛው ስርዓት በነፃ አውጪ ስም ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ እንዲሁም ከዛም በፊት የሚከተለው የተሳሳተ ሃገር የመገነጣጠሉንና ብሔራዊ ጥቅምን አሳልፎ የመስጠቱን እኩይ ተግባር መመልከት የተለመደና የቀን ከሌት ክንውናቸው መሆኑ በሃይል ስልጣን ከያዙበት ጊዜ ጀምሮ የሚታይ እውነታ ነው፡፡
ከምስረታው ጀምሮ ይዞት የተነሳው የኢትዮጵያን ሉዋላዊነት የማፍረስና የመበተን አላማውን መተግበር የጀመረው በወቅቱ የነበረውን ሰራዊት በመውጋት ሃገራችን ያለ ባህር በር እንድትቀርና በኢትዮጵያዊነት የታነፀውን ዘመናዊ የወታደር ሀይል በትኖ በምትኩ የአንድ ብሄር የበላይነት የሚታይበት፣ ብሔራዊ ስሜት የሌለው፣ በህዝብ ላይ አንግሰው ያሻቸውን ሲገሉ፣ ያሻቸውን ሲያስሩ እነሆ አሁን ያለንበት ደርሰናል፡፡ በመሰረቱ ይህ እኩይ ስርዓት በኢትዮጵያዊነት ላይ ካለው የመረረ ጥላቻ የተነሳ አብረው የመሰረቱትንና በኢትዮጵያዊነት ላይ ፅኑ አቋም የነበራቸውን ባልንጀሮቻቸውን ሳይቀር እያስወገዱና እያባረሩ በምግባር የሚመቻቸውን በተለይ በህዝብና በሃገር ላይ የጠለቀ ጥላቻ ያላቸውን አስከትለው የጥፋት ዘመናቸውን ቀጥለውበታል፡፡ በተለይ የመንግስትነትን ስልጣን ከያዙ በኋላ ከስልጣን በተጨማሪ በገቢ እራሳቸውን ለማጠናከር ከኢትዮጵያ ህዝብ በዘረፉት ሃብትና ንብረት በትግራይ ህዝብ ስም ባቋቋሙት ‘ኢፈርት’ ሃገሪቱን ጫፍ እስከ ጫፍ በመቆጣጠር የንግዱን መስክ በበላይነት በመያዝ ገቢና ወጪው የማይታወቅ ትልቅ የሃብት ምንጭ በመፍጠር የአገሪቱን የትኛውንም የንግድ እንቅስቃሴ በበላይነት ይዘው ነግሰውበታል፡፡ በተለያየ መስክ ከሚፈፀመው የሰብዓዊ መብት ረገጣ በተጨማሪ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው በመስጠት ወይም ገንዘብ የሚያስገኝላቸውን ሁሉ በመዝረፍና በማሸሽ፣ ምስኪኑ ህዝብ በዜግነቱ ሊያገኝ የሚገባውን ብቻ ሳይሆን በስሙ ተለምኖ የመጣውን ሁሉ በመንጠቅ ብዙሃን በርሃብ በሚሰቃይበት ሃገር ለአራት ለአምስት ትውልድ የሚበቃ ሀብት አሽሽተዋል፡፡
ከምርጫ 1997 ዓ.ም በፊት በተወሰነ መጠን እራሳቸው ላወጡት ህገ-መንግስት ተፈጥሯዊ ባህሪያቸው ቢያስቸግራቸውም ህጋዊ መስሎ ለመታየት የሚሞክሩበት ሁኔታዎች ይስተዋሉ ነበር፡፡ በዝያን ወቅት ጋዜጠኞች ምንም እንኳን ፍርድ ቤት መመላለስ የእለት ከእለት ስራቸው ቢሆንም ከአሁን በተሻለ የህትመት ውጤቶች በቁጥርም በይዘትም የተሻሉ ነበሩ፡፡ በሌላም በኩል ይህው እኩይ ስርዓት ህግን ከመሻሩ በፊት የፓርላማ ጀሌዎቹን ሰብስቦ ሊሽር ባስበው ህግ ላይ ሌላ ህግ ሲያወጣ ታይቷል፡፡ ከዚህ በፊት ህውሃት በአመለካከትም ይሁን በግል ጥላቻ የራሱን ሰዎች ሲበላ ከቻለ አንዱን በአንዱ ላይ አስነስቶ በማጫረስ አልያም በአደባባይ በደላቸውን እንዲናዘዙ በማስገደድ ከተጠያቂነት እራሱን ሲከላከል መቆየቱ አንድም እራሱን ላለማጋለጥ አልያም በሃገርና በህዝብ ላይ ለሚፈፅማቸው በደሎች ሰርዞም ደልዞም ህግዊ ለመምሰል ይጥራል፡፡
ከምርጫ 1997 በኋላ ያለው በፊት ከነበረው ጋር ማነፃፀር ይከብዳል፡፡ እጅግ ብዙ እርቀት ወደ ኋላ የመመለስ ያህል ነው ፥ምክንያቱም በዛን ወቅት በተፈጠረው በጣም ጠባብ አጋጣሚ ህዝቡ ለስርዓቱ ያለውን ጥላቻና ለውጥ ፈላጊነቱን እንዲሁም ወያኔዎች በተግባር የማያውቁትን ዴሞክራሲ ህዝቡ ሲዘምርላቸው፣ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ከነሱ እንደሚሻል ሲያሳያቸው፣ በተቃራኒው ደግሞ ይበጁኛል የሃገሬን እና የእኔን ህልውና ይጠብቁልኛል፣ ብሩህ የነፃነት ጊዜ ያመጡልኛል ብሎ የሚላቸውን እንደራሴዎቹን ሲመርጥ ለአፍታ በዓይነ ህሊናችን እናስታውስ፡፡
ከዚህ በኋላ ያለችው ኢትዮጵያ የግል የህትመት ውጤቶች ሙሉ በሙሉ በማፈን በሀገራችው፥ በሞያቸው ይህ ነው የሚባል ለውጥ ማምጣት የሚችሉ ጋዜጠኞችን በማሰርና በማሳደድ፣ ለሃገራችን ክብርና ለህዝቧ ነፃነት የሚሟገቱ የሚታሰሩባት፣ የሚገደሉባት ወይም በሃገራቸው በነፃነት የመኖር መብት አጥተው የሚሰደዱባት አልያም የነሱ የሆነውን በሌሎች ተቀምተው የመከራ ቀንበር ከብዶ በግዞት የሚኖርባት ስትሆን ለኢምንት ባለ ጊዜዎች ግን የምድር ገነት ሆና ያሻቸውን የሚሆኑባት የግል ርስት አድርገዋታል፡፡
ለዚህ ሁሉ በሃገርና በህዝብ ላይ ለሚደርሰው እንግልትና መዋከብ ምንም እንኳን የመንግስትን እርካብ የተቆናጠጡት ’ገዢዎቻችን’ ከተፈጥሮ ባህሪያቸው አንፃር የፈለጉትንና ያሻቸውን ቢያደርጉም በየግዜው በህዝብ ላይ የሚያደረሱትን ሰቆቃ የየሰሞኑ መነጋገሪያ ከማደረግ በዘለለ ህዝብ እንደ ህዝብ በደል በቃኝ፣ ግፍ በቃኝ፣ መሰደድ በቃኝ፣ መታሰርና መገረፍ በቃኝ፣ ከሃብትና ከቀዬ መፈናቀል በቃኝ ብሎ ለለውጥ እንዲነሳ በህብረት ከመስራት ይልቅ የነሱን መበታተንና መሰነጣጠቅ አውርተን በድክመታቸው ሳንጠቀም መልሰው ተደራጅተው መብትና ክብራችንን ሲገፉንና ሲፃረሩን እናያለን፡፡ ሃገርና ህዝብን ከዚህ እኩይ ስርዓት መታደግን ለተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ብቻ ትተን በሰሞነኛ የወያኔ የጭካኔ ገድል ላይ ሻይ እየጠጣን ስናነሳና ስንጥል ከወሬ የዘለለ ተግባራዊ የትግል እንቅስቃሴ ውስጥ ሳንገባና የታደሉት ለሃገራቸውና ለህዝባቸው የሚከፍሉትን መስዋዕትነት የሚሰሩትን ታላቅ ስራ ስናፈርስና ስንክብ የዜግነት ግዴታችንን በአግባቡ ሳንወጣ ’ለገዢዎቻችን’ መሳሪያ ሆነን እንዳንቀር መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ በነፃነት በመኖር የምንቀድማቸው ሃገራት ሰልጥነው በዴሞክራሲያዊ ስርዓትና መልካም አሰተዳደር የህዝቦቻቸውን ሰብዓዊ መብት ለማስጠበቅ ደፋ ቀና በሚሉበት በዚህ ዘመን የኋሊት የሚጓዘው ከዘመኑ ጋር መዘመን ያቃተው ወያኔ ከብዙ ዘመናት በፊት በነበረው አስተሳሰብና የሃይል አገዛዝ ተሸብቦ ያላስነባው ህዝብ፣ ያልጣሰው ህግና ስርዓት፣ ያላፈረሰው አንድነት፣ያላዋረደው የህዝብ ስብእና፣ ያልገባበት የእምነት ተቋም፣ ያልበተነው የሞያ ማህበራት፥ ያልገደለው፣ ያላሰረውና ያላስለቀሰው የህብረተሰብ ክፍል የለም፡፡
*–ከላይ ወያኔ ከደደቢት እስከ ቤተ-መንግስት ጸረ-ኢህአዴግ ተብሎ የፈረጀውን አመለካከት ለመምታት የተጠቀመባቸው ስትራቴጅዎች በሙሉ ሁሉንም ተግባራዊ እያደረጋቸው ይገኛል፡፡ በሃገራችን ታሪክ ታይቶ እና ተከስቶ የማያውቅ የሽፍቶች አሸባሪ መንግስት በተለያየ ስልት ኢትዮጵያውያንን መከራቸውን እያሳየ ይገኛል:: ይህ ወንበዴ መንግስት ማፊያዊ ስልቶችን በመጠቀም የተለያዩ ሽብሮችን እየፈጸመ ነው:: መውደቂያው የደረሰው እና በቋፍ ላይ ያለው ይህ መንግስት ስለ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን የሚያስቡ ሰዎችን የሚዋጋበት ስልቱ የህዝብ ንብረት እና ገንዘብ በመጠቀም ስልጣኑን ላለማጣት እየተራወጠ ይገኛል:: ይህንንም ለመዋጋት ድፍን ኢትዮጵያዊ ዘር ሃይማኖት ቀለም ወ.ዘ.ተ. ሳይለይ በአሁን ሰአት በጋራ ’ድምጻችን ይሰማ’ እያለ ለመብቱ እና ለነጻነቱ እየታገለ ነው:: በአሁኑ ወቅት አዛዥና ታዛዥ በውል በማይታወቅበት የወያኔ ስርዓት ዘመኑ እያከተመ መሆኑን ከሚሰራቸው ስራዎች መገንዘብ አይከብድም፡፡ ህግ ማሰከበር ያለበት አንድ መንግስት ላወጣው ህግ መገዛት የማይችልበት ደረጃ ከደረሰ ህልውናው አደጋ ውስጥ ለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡ ለዚህ መብቱን በወያኔ የተነጠቀው ህዝብ የህገ-መንግስቱን አንቀፅ እያሳየ ’የህግ ያለህ’ ሲል መደመጡ፡ በግምት የሚመራን ስርዓት የመጨረሻው ጠርዝ ላይ መቆሙን አመላካች ነው፡፡ –*
ኢትዮጵያ፥ ሀሳብን በነፃነት ያለፍርሀት መግለፅ የማይቻልባት፤ የዜጎች የኑሮ ደረጃ ከዕለት ዕለት እየተባባስ የሚሄድባት፤ ዘማናዊ የመረጃ ግንኙነቶች (information technology) ሆን ተብለው የታገዱበት፤ የህዝቦቿን መከባበርና አንድነት በዘር ጥላቻና በሀይማኖት ለመከፋፈል አገዛዙ የሚጥርበት፤ ዜጎች አላግባብ የሚታሰሩባት፣ የሚገደሉባት፤ ዜጎች በከፍተኛ ሁኔታ የሚሰደዱባት፤ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ የማይካሄድባት፤ ዜጎች ከመኖሪያቸውና ቀዬአቸው የሚፈናቀሉባት፤ ለሕግ ተገዢ ያልሆነ መንግሥት ያለባት፤ ዜጎች የገዢው ፓርቲ አባል ካልሆኑ በነፃነት ሠርተው መኖር የማይችሉባት፤ በተግባር ያልዋለ ህገ-መንግሥት ያላት፤ ነፃ ሚዲያ የሌለባት፤ ዜጎች ለሀብት ንብረታቸው ዋስትና የማያገኙባት፤ ህዝባዊ መንግሥት የሚናፍቅ ህዝብ ያለባት፤ በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም ተቋማት የገዢው ፓርቲ ፖለቲካ መጠቀሚያ የሆኑባት፤ ዜጎች በአስተሳሰብ እና በዕውቀት እየቀጨጩ፣ ቤቶች በቁመታቸው ማደጋቸው እንደዕድገት የሚቆጠርባት ሀገር ሆናለች።
እለት እለት እየተጠናከረ በመጣው አፈና ምክንያት ፌስቡክን እና ሌሎች ሶሽያል ሚድያዎች እንደመተንፈሻ እና መንግስትን ለመታገል እንደዋነኛ መደራጃ እያገለገለ እንደሚገኝ ግልፅ ነው። ታዲያ ሁሉንም ነገር ካላፈኑ እንቅልፍ የማይወስዳቸው ወያኔዎች የፌስቡክ ነገር ከቁጥጥራቸው እንደወጣ ስለተገነዘቡ ፌስቡክ የሚፈጠሩ ግሩፖችን፥ገፆችንና የግለሰብ ፕሮፋየሎችን እየተከታተሉ ከመዝጋት ባሻገር ፀረ-ፌስቡክ የሆነ ዘመቻ ከጀመሩ ውለው አድረዋል። እስከአሁን ፀረ-ፌስቡክ የሆኑ የፕሮፓጋንዳ ስራዎች በኢቲቪ፥ እና በተለያዩ ሚድያዎች ሲደሰኩሩ ሰንብተዋል።
በአሁኑ ወቅት ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚጠይቀዉ አንድ ጥያቄ ነዉ። ይህም የአንድነትና ተባብሮ የመስራት ጥያቄ ነዉ። ይህንንም ጥያቄ ህብረተሰቡ በተገኘዉ መድረክ ላይ ሁሉ ሳያሰልስ እያነሳዉ ይገኛል። ከዚህ አኳያ ለዚህ ህዝባዊ ጥያቄ ሁሉም በጉዳዩ ያገባኛል የሚሉ ወገኖች ሁሉ ጊዜ ሳይሰጡ በመገናኘትና በዚህ ታላቅ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ እጅግ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተዉ ሊወያዩበትና ሊመክሩበት አልፎም መፍትሄ ማስቀመጥና ይህንኑም ለማስፈጸም በጋራ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል።
ዘረኛው የወያኔ አስተዳደር በአገራችን ኢትዮጵያና ህዝቦችዋ ላይ የሚያደርሰውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ ነፃነት ገፈፋና መብት ረገጣን ለማጋለጥ፣ ለማስቆምና ሥርዓቱን አስወግዶ ሁሉን አቀፍ በሆነ መንግስት ለመተካት በትጥቅ እና በሰላማዊ ትግል እንደ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሽግግር ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና ሌሎችም የሚያካሂዱት ትግል እንደቀጠለ ነው። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በየግዜው በሚሰነዝረው ጥቃት የወያኔ መንግስት እንዳሳሰበው በየግዜው ከሚያስማው ሮሮ መረዳት ይቻላል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት ይህንን ብልሹ ሥርዓት ለማስወገድና ህዝብ በመረጠው መንግስት ለመተካት በሚደረገው ትግል የበኩሉን አስተዋፆ ለማድረግ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በዚህም መሰረት በተለያዩ አጋጣሚዎች የተነሱ ተደጋጋሚና ወሳኝ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያና ማሻሻያዎችን አድርጓል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት የወያኔን ጸረ-ኢትዮጵያ አገዛዝና የዘረኝነት ስርዓት አስወግዶ የኢትዮጵያ ህዝብ በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ በመረጠው ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመተካት የሚታገል ህዝባዊ የፖለቲካ ተቋም እንጂ የሽግግር መንግስት አይደለም ። የሽግግር መንግሥት ስንል ደግሞ የወያኔ አገዛዝ ከተወገደ በኋላ የሚተካ ሁሉን አቀፍ የሆነ፥ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ መንግስት እስኪቋቋም የሚያገለግል ጊዜያዊ አስተዳደር ነው።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ም/ቤትም ከተነሳለት ህብረተሰቡን የማስተባበር አላማ በመነሳት ከተባባሪ አካላት ጋር በመሆን፤ ለህብረተሰቡ ጥያቄ ቀጥተኛ እና ቆራጥ ምላሽ ለማሰጠት፤ ያለዉን ስርአት በማስወገድ ሂደትና ስርአቱም ከተወገደ በኋላ ስለሚተካበት ሁኔታ፤ ሁሉም ባለድርሻ አካሎች አማራጮቻቸውን የሚያቀርቡበት “ትግሉም የጋራ ድሉም የጋራ” በሚል መርህ ዙርያ ታላቅ ሁሉን አቀፍ የምክክር ጉባኤ በሚቀጥለው ወር ጁላይ 2013 (እኤአ) በዋሽንግተን ዲሲ ላይ እየተሰናዳ ይገኛል። የኢትዮጵያን አንድነትና ሉዓላዊነት፥ የዜጎችን ሰብዓዊ መብት ለማስከበር ሁሉን አቀፍ ህዝባዊ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም ቅድመ ሁኔታዎችን የማመቻቸት ትልቅ ስራ ይጠብቀናል።
ይህ ከላይ ያነሳሁትና ተነግሮ የማያልቀው በህዝብ በሃገር ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ በወያኔ ተንኮል ብቻ ሳይሆን የኛም ግፍና በደልን የመሸከም አቅም ወይም እንደ ሰው መብታችንን የማስጠበቅ፣ ህልውናችንን ያለማስደፈር ወይም በውርደት መኖር በቃኝ ብለን ሃላፊነታችንን ሳንወጣ እንዲሁ ከድርጅት ድርጅት ስንላተም፣ ከፓርቲ ፓርቲ ስንከለስ በተዘዋዋሪ የወያኔ መሳሪያ ሆነን በህዝባችንና በሃገራችን ላይ የሚደርሰውን በደልና እንግልት ትኩረት ሰጥተን መንቀሳቀስ አለብን፡፡
ስለሆነም ኢትዮጵያንና ህዝቧን ለመታደግ በየትኛውም የትግል መስክ ተሳትፎ በማድረግ ለነፃነት፣ለፍትህ እና ለእኩነት በሚደረገው ትግል ውስጥ የየራሳችንን አሻራ ለማሳረፍ ለተግባራዊ ትግል እንትጋ፡፡
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ኦባማ – “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ”

“ግብረሰዶማዊነት ወደፊት!”
obama in senegal


በድጋሚ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አፍሪካን እየጎበኙ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በሴኔጋል ጉብኝት ባደረጉት ወቅት የግብረሰዶማውያን መብት ሊከበር እንደሚገባው አስታወቁ፡፡ የአገራቸው ጠቅላይ ፍርድቤት ሰዶማውያንን የሚደግፍ ውሳኔ ሰሞኑን በማሳለፉ ደስታቸውን ገለጹ፡፡ የሴኔጋሉ አቻቸው ግብረሰዶማውያን እንዳይወነጀሉ ለማድረግ አገራቸው ዝግጁ አለመሆኗን ተናገሩ፡፡
ሰሞኑን በአፍሪካ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ፕሬዚዳንት ኦባማ ጉብኝታቸውን በጀመሩባት ሴኔጋል የግብረሰዶማውያንን መብት በተመለከተ ለአፍሪካውያንና ለመሪዎቻቸው ማብራሪያና “ትምህርት” ሰጥተዋል፡፡ “መንግሥታት ዜጎቻቸውን እንዴት ሊያስተናገዷቸው ይገባል፤ ሕጉስ እንዴት ሊያያቸው ይገባል ለሚለው ጥያቄ መልሱ ሁሉም ሰው በእኩልነት ሊስተናገድ ይገባዋል” በማለት “ግብረሰዶማዊነት ወደፊት” የሚያስብል ንግግር አድርገዋል፡፡
አፍሪካን እየጎበኙ የሚገኙት ኦባማ የአገራቸው ጠቅላይ ፍርድቤት የግብረሰዶማውያንን መብት ሊያስከብር የሚችል ውሳኔ ማስተላለፉ እንዳስደሰታቸው በጉብኝታቸው ወቅት ጠቁመዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ያስተላለፈው ውሳኔ ለጋብቻ መጠበቅ ከለላ የሚያደርገውን Defense of Marriage Act (DOMA) የተባለው ሕግ ለወንድና ሴት ተጋቢዎች ብቻ በማለት ያስቀመጠው ከለላ የግብረሰዶማውያንን መብት ይጻረራል በማለት ነበር፡፡ ስለሆነም በፍርድቤቱ ውሳኔ መሠረት  በተመሳሳይ ጾታዎች መካከል የተፈጸመ “ጋብቻ” ከፌዴራል መንግሥት የሚሰጡ ጥቅማጥቅሞችን ሊያስከለክል አይገባም በማለት ወንድ ሚስትም ሆነ ሴት ባል ያላቸው ሁሉ የጥቅሙ ተካፋይ እንዲሆኑ ፈቅዶላቸዋል፡፡ እንዲሁም በካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት የሰዶማውያን ጋብቻ እንዲቀጥል ፈቃድ የሚሰጥ ውሳኔ ጠቅላይ ፍርድቤቱ አስተላልፏል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በበርካታ የአፍሪካ አገራት ግብረሰዶማዊነት በህግ የሚያስቀጣ ወንጀል ነው፡፡ ከዚህ አንጻር የሴኔጋሉ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል በበኩላቸው ግብረሰዶማውያን እንዳይከሰሱ ለማድረግ አገራቸው ዝግጁ አለመሆኗን ተናግረዋል፡፡ “በጣም በመቻቻል” የምንኖር ነን ያሉት የሴኔጋሉ መሪ አገራት ውስብስብ የሆኑ ሕጎችን በራሳቸው ጊዜ በተግባር ላይ እንደሚያውሉ በመጥቀስ የኦባማን ሃሳብ ተግሳጽ በተሞላበት ምላሽ አስተናግደውታል፡፡
በመቀጠልም አገራቸው ሴኔጋል ወንጀለኞችን በሞት መቅጣት ያቆመች መሆኗን በመናገር አሜሪካ ግን ይህንን እስካሁን ተግባራዊ አለማድረጓን በመጥቀስ ኦባማን ተሳልቀውባቸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአሜሪካ ወንጀለኞችን በሞት የመቅጣት ህግ ከ30 በላይ ግዛቶች ውስጥ ተግባራዊ ሲሆን በተለይም በቴክሳስ በሰፊው እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ወንጀለኞችን በሞት መቅጣት እንደገና ከተጀመረ ከ1974ዓም በኋላ የቴክሳስ ጠቅላይግዛት 500ኛዋን ወንጀለኛ ሰሞኑን በመግደል የቀዳሚነቱን ስፍራ ይዞ ይገኛል፡፡

“ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ”

በፈረንሣይ አብዮት አካባቢ ህዝቡ መራቡን በተለይም የፈረንሣይ ጭሰኞች መቸገራቸውና በረሃብ እየተንገላቱ መሆናቸውን የተነገራት ልዕልት ማሪ አንቷኔ (“Qu’ils mangent de la brioche”) “ከራባቸው ኬክ ይብሉ” ብላ መልሳለች እየተባለ ለዘመናት ሲዘበትባት ኖሯል፡፡ ልዕልቲቱ ይህንን ለማለትዋ የተረጋገጠ ነገር ባይሆንም ነጻነት፣ መልካም አስተዳደር፣ ዴሞክራሲ፣ ፍትሕ፣ … ለጠማው የአፍሪካ ሕዝብ ባራክ ኦባማ “የግብረሰዶማውያን መብት ሊከበር ይገባል” በማለት መሠረታዊውን የህዝብ ጥያቄ ችላ ማለታቸው “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ” የማለት ያህል እንደሆነ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ጠቁመዋል፡፡
በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት “ለውጥ” እና “ተስፋ” ቀዳሚ ዓላማቸው አድርገው የበርካታዎችን ቀልብ የሳቡት ባራክ ኦባማ፤ ለአፍሪካ መሠረታዊ ችግር እስካሁን ጆሮ አለመስጠታቸው ብዙ የተባለበት ነው፡፡ ሰሞኑን በአሜሪካ ምክርቤት “ኢትዮጵያ፤ ድኅረ መለስ” በሚል ርዕስ በተደረገው ምክክር የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ የተናገሩትን በድጋሚ ያስታወሱም አሉ፡፡ በወቅቱ አቶ ኦባንግ ያሉት “ኦባማ ለምርጫ በተወዳደረ ጊዜ ጥቂት ደመወዝ የሚከፈላቸው ኢትዮጵያውያን የምርጫ ዘመቻውን ደግፈው ነበር፤ እስካሁን ከኦባማ የሰሙት ነገር የለም” በማለት ነበር፡፡
ከምዕራባውያን የሚመነጨውን ማንኛውንም ነገር – ከፖለቲካ እስከ ማኅበራዊ አመለካከት – ትክክለኛ አድርገው ለሚቀበሉ ግብረሰዶማዊነት ሥልጣኔ ይመስላቸዋል በማለት ለጎልጉል አስተያየት የሰጡ የሃይማኖትና የማኅበረሰብ ሳይንስ ጉዳዮች ምሁር “ጋብቻ” የሚለውን ቃል ለሁለት ወንዶች መጠቀም እርስበራሱ የሚጋጭ ጉዳይ ነው በማለት ተመሳሳይ ጾታ ብሎ ጋብቻ ማለት የተሳከረ አነጋገር መሆኑን አስረድተዋል፡፡ “ይህ የሰዶማውያን መብት ይከበር የሚለው ጉዳይ በሕግ እየጸደቀ ሲሄድ ድርጊቱን ከሃይማኖታቸው አኳያ የሚቃወሙ ሰባኪያን የሃይማኖት ትምህርታቸውን በሚያስተምሩበት ቤ/ክ ይሁን መስጊድ ወይም ምኩራብ ግብረሰዶማዊነትን እየተቃወሙ ሰበካ ማድረግ በህግ የሚያስጠይቃቸው ይሆናል” በማለት ወደፊት ሊመጣ የሚችለውን የማኅበረሰብ ቀውስ ጠቁመዋል፡፡
bush in africaበሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው ወቅት ዳግም የመመረጥ ፈተና የሌለባቸው የአሜሪካ መሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመሆን የአፍሪካን የዱር እንስሳት እየጎበኙ ወደፊት ለሚሠሩት ፕሬዚዳንታዊ ቤተመጻህፍት (ፋውንዴሽን) ፎቶ እንደሚሰበስቡ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው፡፡ የባራክ ኦባማም ጉብኝት ከዚህ የተለየ አለመሆኑ ግልጽ ሲሆን “የአፍሪካ ልጅ” እየተባሉ ሲሞካሹ የኖሩት ፕሬዚዳንት ዛሬ ደቡብ አፍሪካ ሲገቡ ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ ገጥሟቸዋል፡፡ ቅዳሜ የክብር ዶክትሬት በሚቀበሉበት የዮሐንስበርግ ዩኒቨርሲቲም ተመሳሳይ ተቃውሞ ይጠብቃቸዋል፡፡
ዛሬ ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ደቡብ አፍሪካውያን “ይቻላል” (Yes! We can!) ለሚለው የኦባማ የምርጫ መፈክር “አትችልም!” (“No, You Can’t Obama,”) የሚሉ መፈክሮችን በመያዝ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡ “ኦባማ የመጣው አፍሪካንና ደቡብ አፍሪካን ለመዝረፍ ነው” በማለት ጠንካራ ተቃውሞውን የገለጸው አንዱ ተሰላፊ “አፍሪካውያን በብዙ መልኩ እየተሰቃዩ እያለ እርሱ ግን የአፍሪካን ሐብት፤ ወርቅ፣ አልማዝ፣ … ለመዝረፍ ነው የመጣው” ብሏል፡፡obama s africa
የዴሞክራሲ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕ፣ … ዕጦት ላንገላታውና በአምባገነኖች መዳፍ ሥር ለሚሰቃየው የአፍሪካ ሕዝብ በቃላት እንኳን ድጋፋቸውን ከመስጠት እስካሁን የተቆጠቡት ኦባማ አሜሪካ በአፍሪካም ሆነ በሌሎች አገሮች ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ፍላጎቱ እንደሌላት በማያወላውል መልኩ ያረጋገጠ መሆኑ የብዙዎች ግንዛቤ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፕሬዚዳንቱን የሥልጣን ኃይል ጥያቄ ውስጥ የሚጥልም ነው፡፡
በአውሮጳ የፖለቲካ ምጣኔሃብት ተመራማሪ የሆኑ እንደሚሉት “አሜሪካኖች እንደ ህወሃት/ኢህአዴግ ዓይነቱን አምባገነናዊ አገዛዝ እስኪያስመልሰው ድረስ በዕርዳታ ገንዘብ ካሽሞነሞኑ በኋላ“ኢህአዴግን ምን እናድርገው” በማለት “ምክር ስጡን” እያሉ በሕዝብ ሰቆቃ ላይ ያላግጣሉ፡፡ ሲሻቸውም ደግሞ አፍሪካ ድረስ በመሄድ “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ” በማለት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን ችግር ያልሆነውን የግብረሰዶማውያን መብት መከበር ይሰብኩናል፡፡ ታዲያ ለዚህ ልግጫ መልሳችን መሆን የሚገባው “ራሳችንን ነጻ እናወጣለን፤ ነጻነታችንን አንለምንም፤ አሜሪካ ግን በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት እንድትሆንብን አንፈልግም” በማለት አቶ ኦባንግ ሜቶ ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ ምክርቤት በተካሄደው ምክክር የተናገሩትን ዓይነት ቁርጠኝነት ነው በማለት አስተያየታቸውን ደምድመዋል፡፡
obama africa trip100ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣው የኦባማ የአፍሪካ ጉብኝት በአሁኑ ጊዜ በበጀት ቀውስ ምክንያት በርካታ ሠራተኞች ደመወዛቸው እየተቆረጠ ባለባት አሜሪካ አነጋጋሪ መሆኑን ዋሺንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡ የደኅንነት ሰዎችን እንዲሁም 14ሊሞዚን፣ 56 ጥይት የማይበሳቸው ድጋፍ ሰጪ  መኪናዎች፣ ሙሉ የህክምና ባለሙያዎችን የያዘና ጀቶችን የጫነ መርከብ … ለፕሬዚዳንቱና ለቤተሰባቸው ጥበቃ በማድረግ ሥራ ላይ እንደሚውሉ ጋዜጣው ያብራራል፡፡
ፕሬዚዳንት ኦባማ በደቡብ አፍሪካ የሁለት ቀን ቆይታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሰኞ ወደ ታንዛኒያ ያመራሉ፡፡ የአባታቸው የትውልድ አገር ነው የሚባለውን ኬኒያ ሳይረግጡ በዚያው ወደ አገራቸው እንደሚያቀኑ የጉዞ መርሃግብራቸው ያስረዳል፡