Friday, May 31, 2013

ጥቁር ለባሾችን እናመሰግናለን! (ሰማያዊ ፖርቲ)



ሰማያዊ ፖርቲ ከግንቦት 15 እስከ 17 ጥቁር አልባሳት በመልበስ እንዲሁም ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት ጽ/ቤት ፊትለፊት የተቃውሞ ሠልፍ መጥራቱ የሚታወስ ነው፡፡ በነዚህ ቀናት ጥቁር አልባሳት በመልበስ ፓርቲው ላደረገው ጥሪ ህዝቡ ያደረገው ተሣትፎ የሚደነቅ ነው፡፡
በመሆኑም ይህ የህዝብ ተሣትፎ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን በመጪው እሁድ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በሚካሄደው ታላቅ ህዝባዊ የተቃውሞ ሠልፍ ጥቁር አልባሳት መልበስ አስገዳጅ ያለመሆኑ እና ማንኛውም አልባስት መልበስ የሚቻል መሆኑን እየገለጽን በዕለቱ የተቃውሞውን ሠልፍ ደማቅ ለማድረግ ከሠልፉ ዓላማ ጋር ተዛማጅነት ያላቸውን የተለያዩ መፈክሮችና መልዕክት አስተላላፊ ነገሮች በቡድንና በተናጥል በመስራት እና በማዘጋጀት በዕለቱ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሃላፊቱን እንዲወጣ ፓርቲው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
Addis Ababa, Ethiopia a call for demonstration

No comments:

Post a Comment