Sunday, March 30, 2014

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በሰሜን ጎንደር ላይ የአካባቢውን ማሕበረሰብ የማንቃት፣ የማደራጀትና የመቀስቀስ ተግባር


Imageበሰሜን ጎንደር በላይ አርማጭሆ ትክል ድንጋይ አካባቢ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በራሪ ወረቀት ተበተነ::
በሰሜን ምዕራቡ የሀገሪቱ ክፍል ተሰማርቶ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ተከታታይና ቀጣይ የሆኑ አውደ ውጊያዎችን በመፈጸም የወያኔን ጦር እያሽመደመደው ከመሆኑም በተጨማሪ ግንባሩ በአሁኑ ሰዓት የአካባቢውን ማሕበረሰብ የማንቃት፣ የማደራጀትና የመቀስቀስ ተግባር ላይ ተሰማርቶ እየሰራ ሲሆን የደርጅቱን ዓላማና ፕሮግራም ያነገቡ በራሪ ወረቀቶችንም በብዛት በማዘጋጀት ወደ ሕብረተሰቡ እንዲደርሱ ተግቶ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት በመጋቢት 20 ቀን 2006 ዓ/ም በሰሜን ጎንደር በላይ አርማጭሆ ወረዳ ትክል ድንጋይ አካባቢ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርን ዓላማና ፕሮግራም ያነገቡ በራሪ ወረቀቶች በብዛት የተበተነ ሲሆን በአካባቢው ነዋሪ የማሕበረሰብ ክፍሎች እነዚህ በራሪ ወረቀቶች በብዛት የተሰራጩ ከመሆኑም ባሻገር ወረቀቶቹ ባልተዳረሱበት አካባቢ ለማሰራጨት ነዋሪዎች ተግተው በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኙ ሪፖርተራችን ከስፍራው ያደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ይህንኑ በራሪ ወረቀት ወደ ሕብረተሰቡ በፍጥነት እንዲሰራጩ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል በሚልና ከዚሁ ጋር ተያያዥነት ባለው ጉዳይ በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች በገዢው ቡድን ታጣቂ ሃይሎች እየታደኑ ለእስር መዳረጋቸውን እንዲሁም በትክል ድንጋይና አካባቢዋ ከፍተኛ ውጥረት መንገሱን መረጃው ጨምሮ ገልጿል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በላይ አርማጭሆ ወረዳ ትክል ድንጋይ አካባቢ የተበተነው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በራሪ ወረቀት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በሰፊው እንዲሰራጩ የአካባቢው ወጣቶች በራሪ ወረቀቶቹን እያባዙ በመበተን ላይ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር (ኢ.ሕ.አ.ግ) የወቅቱን የፖለቲካ ትኩሳትና ተጨባጭ የወያኔ እንቅስቃሴዎችን መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለበለጠ የፀረ- ወያኔ ትግል የሚያነሳሱ በራሪ ወረቀቶች በማሰራጨትና የትጥቅ ትግሉ የደረሰበትን የዕድገት አቅጣጫና አናሳው የወያኔ ቡድን በሕዝብ እና በሀገር ላይ እየፈጸመ ያለውን ስውር ደባ በማጋለጥ በኩል ጉልህ የፕሮፖጋንዳ መሳሪያ በመሆን ሕዝብን ወደ ትጥቅ ትግሉ ጎራ እንዲቀላቀሉ ተነሳሽነትን የፈጠረ መሆኑ የአካባቢው ነዋሪ ማሕበረሰብ መናገራቸውን የሪፖርተራችን መረጃ ያስረዳል።
በመጨራሻም በራሪ ወረቀቶቹ በተሰራጩባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በስፍራው ለሚገኘው ሪፖርተራችን እንደገለጹለት ከሆነ በራሪ ወረቀቶቹ ወቅታቸውን የጠበቁ የሁሉንም ሕብረተሰብ ብሶትና ምሬት ገላጭ መሆናቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸው ለግንባሩ የሀገር አድን ጥሪ ምላሽ የምንሰጥበት ወቅት ላይ በመሆናችን የግንባሩን ሠራዊት በመቀላቀል የዜግነት ግዴታችንን ለመወጣት ቆርጠን ተነስተናል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

Interview with Dr Abeba Fekade

https://www.youtube.com/watch?v=tvcC4ZM-AiU&list

በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት… የህወሃት ሰዎች ጉድ!


በዝርፊያ ወንጀል ተጠርጥረው በተከሰሱ የደኅንነት ሠራተኞች ላይ ምስክሮች ተደመጡ
በውጭ ዜጋ ላይ ዝርፊያ በመፈጸም ወንጀል ተጠርጥረው በተከሰሱ የደኅንነት ሠራተኞች ላይ ምስክሮች መደመጥ ጀመሩ፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የአገር ውስጥ ደኅንነት ሠራተኛ በሆኑት አቶ ዮሐንስ ኪሮስ አብዩና በአቶ በኩረ ጽዮን አብረሃ ዜና፣ እንዲሁም ሾፌር መሆኑ በተገለጸውና ተባባሪ ነው በተባለው የኑስ አብዱልቃድር መሐመድ ላይ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ያቀረባቸውን ምስክሮች መስማት የጀመረው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት መጋቢት 18 ቀን 2006 ዓ.ም. ነው፡፡
ክሱ እንደሚለው፣ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ከአሥር ወራት በፊት ግንቦት 14 ቀን 2005 ዓ.ም. ከምሽቱ 12፡30 ሰዓት ሲሆን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 19 ልዩ ቦታው ደንበል ሲቲ ሴንተር ሕንፃ አካባቢ፣ ሚስተር ካሊድ አዋድ የተባሉ የሳዑዲ ዓረቢያ ዜግነት ያላቸውን ግለሰብ ያገኟቸዋል፡፡
ግለሰቡን ሲፈትሿቸው 1,200 ዶላርና 1,600 የሳዑዲ ሪያል አግኝተው ከወሰዱ በኋላ፣ ወደ ካራማራ ፖሊስ ጣቢያ ወስደው እንዳሳደሯቸው ክሱ ያስረዳል፡፡ በማግሥቱ ግንቦት 15 ቀን 2005 ዓ.ም. የግል ተበዳይን ቤታቸው በመውሰድ ቤታቸውን በመበርበርና የተቆለፈ ሳምሶናይት በመስበር 8,000 የሳዑዲ ሪያልና 2,000 ዶላር፣ በድምሩ ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲቀየር 106,880 ብር ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸውንም በክሱ ተጠቁሟል፡፡
ሾፌር መሆኑ የተገለጸው የኑስ አብዱልቃድር የተባለው ተርጣሪ ደግሞ ከሁለቱ ተጠርጣሪዎች ጋር በመመሳጠር፣ የግል ተበዳይ የሆኑትን የሚስተር ካሊድ አዋድን ቦታና እንቅስቃሴ በመጠቆም፣ እንዲሁም የተሽከርካሪ አገልግሎት በመስጠትና በወንጀሉ ተሳትፎ በማድረግ 13,000 ብር ለግል ጥቅሙ ማዋሉን ክሱ ያብራራል፡፡
Corruption by TPLF securities
የደኅንነት ሠራተኞቹ የግል ተበዳይን በቁጥጥር ሥር ባዋሉበት ዕለት በግምት ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ሲሆን፣ የተበዳዩ ሠራተኛ መሆናቸው ለተገለጸ ግለሰብ ስልክ ደውለው 100 ሺሕ ብር ካልሰጧቸው ተበዳዩ እንደማይፈቱ መግለጻቸውን የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡
በአጠቃላይ ተጠርጣሪዎቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ፈጸሙት በተባለው ገንዘብ ወስዶ መሰወርና ጉቦ መጠየቅ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው፣ ዓቃቤ ሕግ እንደ ክሱ የሚያስረዱለትን ሦስት ምስክሮች ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡
የዓቃቤ ሕግ የመጀመሪያ ምስክር ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ሾፌሩ ስልክ ደውሎላቸው 100 ሺሕ ብር ካልሰጧቸው ተበዳዩን እንደማይለቋቸው እንደገለጹላቸውና በድጋሚ ከደኅንነት ሠራተኛው በኩረ ጽዮን ጋር በመሆን የተጠየቀውን 100 ሺሕ ብር ወደ 80 ሺሕ እና 50 ሺሕ ብር ዝቅ በማድረግ እንደተደራደሯቸው መስክረዋል፡፡
ሁለተኛው ምስክር የግል ተበዳዩ ሲሆኑ፣ በክሱ ላይ የሰፈረውን ቃል በቃል አስረድተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ቀሪ ምስክር ለመስማት ለሚያዝያ 9 ቀን 2006 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Saturday, March 29, 2014

ኢሕአዴግ ለምን ማኅበረ ቅዱሳንን ማፍረስ ፈለገ?


  • ሥርዐቱ በተለይም መንግሥታዊ ሥልጣናቸውን ለሃይማኖታዊ ተልእኮ የሚጠቀሙ ሓላፊዎችና አማሳኝ የደኅንነት ግለሰቦች አሁን በተያዘው መንገድ ቀጥለው ማኅበረ ቅዱሳንን አላግባብ ወደ መገዳደር ብሎም ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አማሳኝ ግለሰብ ሓላፊዎች ጋራ ተባብረው ወደ ማፍረስ የሚሸጋገሩ ከኾነ ያለምንም ጥርጥር የተቃውሞው ጎራ ይጠናከራል፡፡ ይህም አገሪቱን በልማታዊ ዴሞክራሲያዊ የአውራ ፓርቲ ሥርዐት ለአርባና ኃምሳ ዓመታት እመራለው ለሚለው ገዥው ፓርቲ ግብዓተ መሬት አፋጣኝ ምክንያት ሊኾን እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች ይስማማሉ፡፡
  • በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ሃይማኖታዊና ምጣኔ ሀብታዊ ፍላጎት ያላቸው የገዥው ፓርቲ ባለሥልጣናትና ጥቂት አማሳኝ የደኅንነቱ ሰዎች ተቋሙን አፍርሶና ቤተ ክርስቲያንን በሒደት አዳክሞ በመቆጣጠር አልያም በታትኖ ለፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃን ማስረከብ ቀላል እንደኾነ ያስባሉ፡፡ በአንጻሩ ‹‹በምድር ላይ ሊሳኩ ከማይችሉ ነገሮች አንዱ ይኼ የአፅራረ ቤተ ክርስቲያን ምኞት ነው፤››የሚለው አንድ የቀድሞው የማኅበሩ ሥራ አመራር አባል እንደሚያሳስበው፣ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ የማኅበሩ አባላትና ደጋፊዎች፣ ማኅበሩ በግቢ ጉባኤያት አንፆ መስቀል በአንገታቸው አስሮ የሸኛቸው በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ምሩቃን፣ ኦርቶዶክሳውያን ምሁራንና በማኅበሩ ስኬታማና ተጨባጭ አገልግሎት የቤተ ክርስቲያን ፍቅር ያደረባቸው ምእመናን ኹሉ ለዘመናት እየመነዘሩ ማንኛውንም የቤተ ክርስቲያኒቱን ተግዳሮቶች የሚመክቱበት መንፈሳዊ ኃይል እንዳላቸው በቅጡ መረዳት ያሻል፡፡
  • በርካታ አገራዊ አጀንዳዎች አሉኝ በማለት ሕዝቡን ለሕዳሴ የሚያነሣሣው መንግሥት፣ በተለይም የፀረ አክራሪነቱን ትግል በቅድመ ግንባር እንዲመራ ፖሊቲካዊ ተልእኮ የተሰጠው አካልና ሓላፊዎቹ፣ መካሪ እንደሌለው የእብድ ሥራ ከመሥራታቸውና እጃቸውን ወደ ብልሽት ከመዘርጋታቸው በፊት ነገሮችን በርጋታ ማጤንና በግልጽ ውይይት ማመን ይበጃቸዋል፡፡
Enqu Magazine Megabit Cover(ዕንቊ፤ ቅጽ ፮ ቁጥር ፻፲፬፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.)
ከሰሞኑ ኢሕአዴግ መራሹ ግብረ ኃይል ማኅበረ ቅዱሳንን የማፍረስ እንቅስቃሴውን ከየትኛውም ጊዜ በባሰ አጠናከሮ መቀጠሉ እየተደመጠ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሐቀኛና ዓይናማ አበው ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ዘንድ ዐቃቤ ሃይማኖት ኾኖ የሚታየውና በብዙዎች ምሁራን ዘንድ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የምሁራን ክንፍ (academic wing) መኾኑ የሚታመነው ማኅበረ ቅዱሳን የገዥው ፓርቲ ጥቃት ሰላባ መኾኑ አይቀሬነት እውን እየኾነ መምጣቱ ብዙዎችን እያሳሰበ ነው፡፡
በተለይ ጥቃቱ የማኅበሩ የአስተሳሰብ፣ የመርሕና የስትራተጂ ርትዓተ አእምሮ የኾኑ አመራርና አባላቱ ላይ ማነጣጠሩ ርምጃው ደጅ ላይ ስለመኾኑ ማረጋገጫ ተደርጎ እየተወሰደ ነው፡፡ በኢ.ቴቪ ይዘጋጃል ተብሎ የተነገረውም ዶኩመንተሪ የዚሁ ጥቃት መንገድ ጥርጊያ ተደርጐ መታየት አለበት ይላሉ፤ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ምሁር፡፡

Friday, March 28, 2014

“ለውጡ እንደቀረበ ጥርጥር የለኝም” ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር

ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሁለት ወር በፊት ወደ አሜሪካና የአውሮፓ አገራት ለስራ ጉብኝት ሄደው ነበር፡፡ አሁንም ወደ አሜሪካ ጉዞ ሊያደርጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ፡፡ የአሁኑ ጉዞ አላማ ምንድን ነው?
Eng. Yilkal Getnet Semayawi party chairman with Negere Ethiopia newspaper
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር
ኢንጅነር ይልቃል፡- መጀመሪያ ያደረኩት ጉዞ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም፣ የሰራናቸውን እንዲሁም ወደፊት ልንሰራቸው ያሰብናቸውን ስራዎች፤ ሰማያዊ እንደ አዲስ ኃይል ሲመጣ የቆመላቸው ሀሳቦችና እምነቶች ምን እንደሆኑ ለማስተዋወቅ ታስቦ የተደረገ ነበር፡፡ የአሁኑ ግን ከበፊቱ የተለየና ለሰማያዊ ሊቀመንበር በሚል በቀጥታ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት የተደረገ ግብዣ ነው፡ ፡ የአሁኑ ወጣት የአፍሪካ መሪና ወደፊትም ለአገራቸው መሪ ሊሆኑ የሚችሉ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ጥሩ ስራ የሰሩ፣ በውድድር ከተመረጡ በኋላ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት በሚደረግ ምርጫ መመዘኛዎቹን ለሚያሟሉ ሰዎች የሚሰጥ እድል ነው፡፡ በመመዘኛዎቹ መሰረት በማሸነፌ የአሜሪካ መንግስት ሙሉውን ወጭ ሸፍኖ ለሶስት ሳምንት በአሜሪካ የመንግስት አወቃቀርና ዴሞክራሲን ጨምሮ በተግባር የሚሰጡ ስልጠናዎችን የማግኘትና፣ የአሜሪካ መንግስት ባለስልጣናትም ባሉበት ከተለያዩ ተቋማት ጋርም ለመገናኘት እድል ይኖረኛል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መሪዎች ጋር ተወዳድረው ነው ያሸነፉት ማለት ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አዎ! ግን ሌሎች ያሸነፉ ተጨማሪ ሰዎች ይኑሩ አይኑሩ አላውቅም፡፡ ይህ የፕሬዝዳንቱም ‹ኢኒሸቲቭ› ይመስለኛል፡፡ ለእኔ ግን የተሰጠኝ አዲስ ትውልድ አመራሮች፣ ወደፊትም በአገራቸው መሪ መሆን የሚችሉ፣ ስትራቴጅካሊ የሚያስቡ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይም ሆነው መልካም ስራ ለሰሩ ሰዎች የሚሰጥ ልዩ የጉብኝት እድል ነው፡፡ በአጠቃላይ ውድድርም ተደርጎ የሚወሰድ ነው ማለት ይቻላል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ይህንን እድል ሲሰጥ እርስዎ እንደ መሪም ሆነ ሰማያዊ እንደ ፓርቲ ያሸነፋችሁበትን ዋና ዋና መመዘኛዎች ነግረዋችኋል?
ኢንጅነር ይልቃል፡- ሲመርጡኝ ዝርዝር መረጃዎችን ወስደዋል፡ ፡ መሰረታዊ የሚባሉትን ለምሳሌ ያህል የፖለቲካ ቆይታዬ፣ የትምህርት ዝግጅቴን፣ በፖለቲካው ውስጥ የነበረኝን ተሳትፎ የመሳሰሉትን መረጃዎች ለእጩነት በቀረብኩበት ወቅት ከእኔ ወስደዋል፡፡ ከዛ በኋላ ያስመረጠኝን ዝርዝር መስፈርት አላውቅም፡፡ ነገር ግን ወጣት (እስከ 45 አመት ባለው ውስጥ)፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ መልካም ስራ የሰራ፣ ወደፊትም የአገሩ መሪ ሊሆን የሚችል የሚሉት ዋና ዋና መመዘኛዎች እንደሆኑ አውቃለሁ፡ ፡ ይህም በተለይ ከሰማያዊ አንጻር ከሁለት ነገሮች አኳያ እንድናየው ያደርጋል፡፡ አንደኛው በምስራቅ አፍሪካ ያለውን ፖለቲካና እስካሁን ጠቅልሎ የያዘው ኢህአዴግ ነበር፡፡ ሌላ አማራጭ እንደሌለ አድርጎ ነበር የሚያየው፡፡ ሆኖም እንደዚህ አይነት እድል እንደ አሜሪካ ባለ ትልቅ መንግስት የተቃዋሚ መሪ የተለየ ስራ ሰርቷል ተብሎ ሲጋበዝ ሰማያዊ ፓርቲ አዲሱንና ወደ ፖለቲካ ያልመጣውን ትውልድ ወደ ፖለቲካው ለማምጣት በሚያደርገው ጥረት እንደ አንድ ማበረታቻ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ይህ በሌሎች መስኮች ከምናደርጋቸው የዲፕሎማሲ ስራዎች በተጨማሪ ለሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች በተለየ ይህኛው ግብዣ ሲደረግለት ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
ከአሁን በፊት ለሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በአሜሪካ ኤምባሲ ውስጥ የ35 አገራት ኤምባሲዎች የ‹ኢትዮጵያ ፓርትነርስ ግሩፕ› የሚባለው ሲደረግ በአመታዊ ስብሰባቸው ላይ ዋና ተናጋሪ ሆኜ ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካና ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ዋና የትግል እንቅስቃሴና የወደፊት አላማችን እንዳስረዳ የተለየ እድል ተሰጥቶኛል፡፡ ይህም ለፓርቲው ሌት ተቀን ለሚሰሩ ወጣቶች፣ እንዲሁም ሁል ጊዜም ቢሆን ወጣቱ ተከታይና ጀሌ እግረኛ ከመሆን አልፎ ራሱ ኃላፊነት የሚወስድ፣ መምራትና የራሱን መሪዎች ማውጣት የሚችል ትውልድ መምጣቱን የሚያሳይ መልካም ጅምር ነው፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ከ9/11 እንዲሁም ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ሶማሊያ ውስጥ ባለው ጥቅም ኢህአዴግ ላይ እስከመጨረሻ ግፊት ማድረግ አልቻለም ነበር፡፡ አሁን ለእርስዎና ለፓርቲዎ ይህን እድል ሲሰጥ ለኢህአዴግ የሚያስተላልፈው መልዕክት ምንድን ነው? የተቃውሞ ጎራውም ቢሆን እስካሁን የሚመራው በ1960ዎቹ ፖለቲከኞች ነው፡፡ አሁን የአሜሪካ መንግስት ይህን እድል ለእርስዎ እንደ መሪና ለሰማያዊ እንደ ወጣት ፓርቲ ሲሰጥ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚኖረው አንድምታ ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እንግዲህ ይህን ጉዳይ ህዝቡም ሆነ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ማህበረሰቡ እየተረዳው የመጣ ይመስለኛል፡፡ ባለፈው አርባ አመት በገዥውም ሆነ በተቃዋሚው ያለው በአንድ አይነት እድሜና የግራ ርዕዮት የሚሽከረከር ነበር፡፡ ይህም የኢትዮጵያን ፖለቲካም ሆነ ኢትዮጵያን በሁሉም መመዘኛዎች ወደ ፊት ሊያራምድ አልቻለም፡፡ እንዲያውም ጥላቻ፣ ቂምና ቆርሾ፣ የእስር በእርስ መጠላፍና የዜሮ ድምር ፖለቲካ ሆኖ ቆይቷል፡ ፡ ያ ትውልድ ያላመጣውን ውጤትም ወጣቱ ያመጣዋል የሚል ነው፡ ፡ ኢትዮጵያ የወጣት አገር ነች፡፡ 70 ከመቶ የሚሆነው ከ35 አመት በታች ነው፡፡ ይህ የህብረተሰብ ክፍል በውክልና ደረጃም ሆነ አዲስ አስተሳሰብና ከበድ ያለ ነገር ይፈልጋል፣ ከዓለም ከተለያየ አቅጣጫ መረጃ ያገኛል፣ በአስተዳደጉም አንጻራዊ ነጻነት አለው፣ በአመለካከትም ቢሆን ይህ የህብረተሰብ ክፍል ወደ ፊት እየመጣ ነው፡፡ ከዚህም አንጻር በታክቲክም ሆነ በአመለካከት ይህን የህብረተሰብ ክፍል መደገፍ የሚያዋጣና አይቀሬነቱን የሚያሳይ ይመስለኛል፡፡
ዋናው የኢህአዴግ የፖሊሲ መሰረት ማታለል ነው፡፡ ‹‹እኔ ከሌለሁ ኢትዮጵያ ትበታተናለች፡፡›› በሚል የምስራቅ አፍሪካንም ሆነ የሶማሊያን የሽብር ሁኔታ እንደ ማታለያ እየተጠቀመ፤ እነሱ የስጋት ፖለቲካ ውስጥ መግባታቸውን ስለሚያውቅ እሳት የማጥፋት ስራ ነበር የሚሰራው፡ ፡ ይህ ግን መሰረታዊ መፍትሄ የሚያመጣ ሳይሆን ነገሮችን እያዳፈነ፣ ችግሩን እያባባሰ በመሆኑ እንዲሁም የጠቅላይነት ፖለቲካን ለቀጠናውም ሆነ ለኢትዮጵያ እየጠቀመ አለመሆኑ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ኃይሎች ተረድተውታል፡፡ አማራጭ የፖለቲካ ኃይልና መሰረታዊ የሆኑ የዴሞክራሲ መመዘኛዎችን ማምጣት፣ መሰረታዊ የሆኑ የዜጎች ልማትና ዴሞክራሲ ማፋጠን፣ በአቻነት የተመሰረተ ግንኙነትን ካልሆነ በስተቀር በጉልበትና በጠብመንጃ የሚደረገው አገዛዝ እንደማያዋጣ የተረዱበት ጊዜ ነው፡፡ አሜሪካኖች አባቶቻቸው የሞቱበት ነገር (the ideals of ower founding fa­thers) የሚሉት የሰውን ልጅ መብትና የሰብአዊ መብት ማክበር ለሁሉም አገራት መድሃኒት መሆኑን ራሳቸው አፍጋኒስታንና ኢራቅ ውስጥ በነበሩበት ወቅት አይተውታል፡፡ በየመን፣ በምስራቅ አፍሪካዋ ሶማሊያም ቢሆን ተመሳሳይ የእሳት ማጥፋት ፖለቲካ ለውጥ እንዳላመጣ ተገንዝበውታል፡፡ በየ ደረጃው በህዝብ ተሳትፎ የሚያድግ ዴሞክራሲና በዜጎችም ይሁን በአገራት መካከል በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ግንኙነት መምጣት ካልቻለ አፋኝነት እንዳልጠቀመ የተረዱበት ጊዜም ይመስለኛል፡፡

Wednesday, March 26, 2014

የስልክና ኢንተርኔት ክትትል የHRW ዘገባ


ሂዉማን ራይትስ ዎች ኢትዮጵያ ዉስጥ ይደረጋል ያለዉን የቴሌፎንና የኢንተርኔት ቁጥጥርና ስለላ የተመለከ ዘገባ ይፋ አደረገ።

Symbolbild Iran Cyberattacke Virus Wurm
ዘገባዉ በዉጭ ሀገር መንግስታት ቴክኒዎሎጂ እና በእነሱም ርዳታ እንዲሁም በደረሱበት እድገት ተደግፎ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱትን ሕዝባዊ ድርጅቶች፣ ጋዜጠኞችና የተቃዉሞ ፓርቲ አባላትን፣ ተማሪዎችንና የሙያ ማኅበራት አባሎችን የኢትዮጵያ መንግስት ይከታተላል የሚል ነዉ። በዉጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንንም እንዲሁ ተከታትሎ ስልካቸዉን በመጥለፍ፣ ኮምፕዩተራቸዉን በርብሮ የግል ምስጢራቸዉን ይከታተል በማለት ሂዉማን ራይትስ ዎች ድርጊቱን ኮንኗል። የድርጅቱን ጋዜጣዊ መግለጫ የተከታተለዉ የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል ዝርዝሩን ልኮልናል። በርሊን የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዓለም ዓቀፉ የመብት ተm።ጋች ድርጅት ሂዉማን ራiteስ ዎች ስላወጣዉ ዘገባ ያለዉን አስተያየት እንዲሰጥ በርሊን የሚገኘዉ ዘጋቢያችን በተደጋጋሚ ጠይቆ ነበር ሆኖም የኤምባሲዉ ባልደረቦች መልሰን እንደዉላለን ቢሉም ስቱዲዮ እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ምላሻቸዉን አላገኘንም።

Tuesday, March 25, 2014

ኢህአዴግ ባደባባይ የወደቀውን ፈተና “በጓሮ” አለፈ



ግልጽነትና ተጠያቂነት ፈረዱ ወይስ ተፈረደባቸው?
short eiti eprdf


ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።
የኢህአዴግን የእውቅና ይግባኝ ጥያቄ ተቀብሎ ያጸደቀው የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የሚባለው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ነው። ተቋሙ ኢህአዴግ በ2009 አቅርቦት የነበረውን የእውቅና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ የሰጠው ምክንያት “የመያዶች ህግ የተሰኘው” አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና በአገሪቱ የተተከሉት አፋኝ ህጎች እስካልተወገዱ ድረስ ማመልከቻው እንደማይታይ በማሳወቅ ነበር።
በ2009 ጠ/ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ “መሰዋት” በስተቀር ኢህአዴግ አንዳችም ለውጥ ባላደረገበት ሁኔታ ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 19፤2006 (March 19፤2014) ይኸው እውቅና ሰጪ ተቋም የራሱን ውሳኔ ቀልብሶ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ከውሳኔው ቀናት በፊት በጓሮ የሚወጠን ድርጊት እንዳለ መረጃ ደርሶት የማሳሰቢያ ተቃውሞ ያሰራጨው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘውየሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እንዳለው ከሆነ ከተገለበጠው ውሳኔ በስተጀርባ ሚስ ክሌር ሾርት ከፊት ረድፍ ተቀምጠዋል።

Sunday, March 23, 2014

ሃያ ሦስት የስቃይ፤ የሰቆቃና የእልቂትና ዓመታት



የኢትዮጵያ ህዝብ በፋሽስቱ ህወሓት ብልሹ አስተዳደርና አምባገነናዊ አገዛዝ ስር ወድቆ በኑሮ ውድነትና በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ፣ ሰብኣዊና ዲሞክራሲያዊ መብቱ ተነጥቆ ለአፈናና ለእስራት እየተዳረገ፣ ሉዓላዊ ክብሩ ተደፍሮ ለም መሬቱንና አንጡራ ሃብቱን እየተሸነሸነና እየተቦረቦረ ለባዕድ እየተሸጠ፣ በገዛ ሀገሩ ተፈናቃይና የውጭ እጅ ተመልካች ሆኖ ለስደትና ለእንግልት እየተዳረገ እነሆ ዛሬ ከ23 ዓመት በላይ የሰቆቃ፣ የእልቂትና የመከራ ዓመታት ተቆጠሩ።
ለአለፉት 23 ዓመታት የደፈረሰው ፖለቲካችን ወደ ጭቃነት እየተቀየረ ስለመሆኑም ምንም ምስክር አያሻውም።ፋሽስቱ ወያኔ ከሀገር ሉዓላዊነት እስከ ታሪካችን፣ ከባንዲራችን እስከ እንደ ሕዝብና እንደ ሀገር ያለን ደረጃ መቀመቅ አውርዶታል። አንዳንዶቻችን እንደዚህ ዘመን ትውልድ አባልነታችን ያለፈውን መለወጥ፣ ዛሬን የሰውነት ደረጀችን በጠበቀ ሁኔታ መኖርና ነገንም ላልተወለዱ ልጆቻችን መልክ አስይዞ ለማውረስ ከቁጥጥራችን እየወጣ መሆኑን በግልጽ እንመለከታለን። በሌላ ወገን ወያኔዎቹ የአለፉት 23 ዓመታት የአንድ ጀምበር ያህል አጥረውባቸው፤ ተጨማሪ 40 አመታትን ለመግዛት በማለም ሲንፈራገጡና በቀቢጸ ተስፋ ህዝብን ለማማለል ሲሞክሩ እያየንና እየሰማን ነው። ስንራብ መጥገባችንን ይነግሩናል። ስንታረዝ ደራርበን መጎናፀፋችን ይታያቸዋል። ሀገራችን ከአለም ሀገሮች ተርታ በሁሉም መስኮች ለማለት በሚያስደፍር ደረጃ በማይታመን ፍጥነት እየወጣች ወደ ግርጌ ስትወረወር፤ ወንበዴዎቹ ወያኔወች ግን ሀገራችን ተሞሸረች አማራች ይሉናል። የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲረግጡት የሚደቅን ቅጠል ያህል በመቁጠር ከህግና ከአመክንዮ ውጭ በማን አለብኝነት ሕዝባችንን በንግድ ድርጅቶቻቸው እየገፈፉ እርቃኑን አስቀርተውታል።
ጉጅሌው ወያኔ ሥልጣን ሲይዝ፣ ከፎከረባቸው አንዱ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀን ሶስቴ የሚበላበትን ሁኔት ፈጥሮ ከረሀብ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚገላገልበትን ባዶ ቃል ኪዳን ገብቶ ነበር። ነገር ግን ዛሬ የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀን ሶስቴ አበሳውን እየበላ ይገኛል። ምግብማ ከየት ተገኝቶ! ረሀቡ፣ ጠኔው ከዛሬ ሀያ ዓመት ሁኔታ በሶስት ዕጥፍ ጨምሮ፣ ዛሬ እስከ 25 ሚሊዮን ሕዝብ ጦሙን የሚያድርባት አገር ስለሆነች በየጊዜው የተባበሩት መንግስታትና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ከሚያወጡት መግለጫ መረዳት ይቻላል። ዛሬማ፣ ነጻ ገበያ ብሎ የፎከረብን ነጻነት ተረስቶ የዘይትና የስኳር ዋጋ እስከመቆጣጠር ገብቷል። ከመብራት፣ ውሃና ኔትዎርክም ብሶ ህዝብ በእጦት ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ይገኛል። በቅርቡም በመላ ሃገሪቱ መብራት፣ ውሃና ኔትዎርክ እጦትን አስመልክቶ ሰልፍ ሊወጣ ቅድመ ዝግጅቶች እየተገባደዱ እንደሆነም እየተሰማ ነው። ከዚህ በላይ የጨለማ ጊዜ የለም።
የወያኔ አገዛዝ ለአለፉት 23 ዓመታት የሀገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም አሳልፎ በመስጠትም በተደጋጋሚ ብሄራዊ ክህደት ሲፈጽም የቆየ ቡድን ነው። ይህንን ብሄራዊ ክህደት ሲፈጽም ካለማወቅ፤ ከችኮላ ወይም በደመነፍስ ከመጓዝ የተሠራ ስህተት አይደለም። ከአጠቃላይ የፓለቲካ ስትራተጂውና ግብ ጋር የተያያዘ አካሄድ ስለመሆኑ መስካሪ አያሻም። ፋሽስቱ ህወሓት በህዝብ የተተፋ ቡድን በመሆኑ የሀገሪቱን ፓለቲካና ኤኮኖሚ ለመቆጣጠር የውጭ ኃይሎችን የገንዘብ፤ የወታደራዊና የዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ስለሚሻ ነው የሀገሪቷን ብሄራዊ ጥቅሞች መረን በለቀቀና ድፍረት በተሞላበት መልክ ለውጭ ኃይሎች በየጊዜው አሳልፎ የሚሰጠው።ለዚህም ነው የምግብ እጥረት ያለባት የሀገራችንን ሰፋፊ ድንግል መሬቶቿን ለሀገሪቷ ዜጎች ከልክሎና አፈናቅሎ ለመካከለኛው ምሥራቅና ለእስያ ሀገሮች ልማታዊ ድርጅቶች በነፃ በሚባል ደረጃ እስከ 99 ዓመት በሚደርስ ውል ፈርሞ እየሸጠ የሚገኘው። ሰፊ ለም የድንበር መሬታችንንም ቆርሶ ለባዕዳን በመሸጥ ላይም ለመሆኑ ከሰሞኑ ለሱዳን ተላልፎ የተሰጠው መሬት ማስረጃ ነው።
በርግጥ የተደራረበ ጭቆናና መከራ ያንገሸገሸውና በልቡ የሸፈተው ህዝብ የጥቂት አምባገነኖችና ሰው በላ መሪዎች የባርነት ቀንበር ተሸክሞ ዘላለም መኖር እንደማይችል ግልፅ እየሆነ መጥቷል። በመሆኑም እንደ እሳተ ጎመራ ውስጡ ውስጡን እየተብላላ ቆይቶ ዛሬ ሊፈነዳ የተቀራበውን የህዝብ ዓመፅ መለብለብ የማይቀርላቸው መሆኑን በውል የተረዳው የጉጅሌው ወያኔ ቡድን ከመቼውም በላይ በፍርሃትና በጭንቀት ተውጠው እንዳበደ ውሻ መቅበዝበዝ፣ መወራጨት፣ መናከስና መተራመስ እንደ ጀመሩ በጋሃድ እየታየ ነው። ባለፈው ሳምንት በሰማያዊ ፖርቲ ሴት አመራርና አባላት መሪነት የታየውን አመጽ ተከትሎ ፋሽስቱ ወያኔ የወሰደው እርምጃ ለዚህ በቂ ማሳያ ነው። ሌላው የአዋጅ ጋጋታ፣ የዉሸት እምብልታ፣ ዜጎችን ያላንዳች ምክንያት ማስፈራራት፣ እስር ቤት ማጎር፣ ማሳደድ፣ መግረፍና ማፍን የመሳሰሉ የቀቢፀ ተስፋ እርምጃዎች በግልፅ የሚያሳዩን የስርዓቱን መፈረካከስና የውድቀቱን ዋዜማ መቃረቡን ነው።
ስለዚህ ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህንን በሞት ጣር ላይ ሆኖ እያቃሰተ የሚገኘውን አገዛዝ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመቅበር መፍትሄው በእጃችን ነው ይላል። ግንቦት 7 መፍትሔው ስለጨቀየው ፖለቲካ እያወሩ ፈጣሪ ባመጣው ይመልሰው ማለት አይደለም ብሎ በፅኑ ያምናል። መፍትሔው እርስ በእርሳችን ስንወጋገዝ መኖርም ሳይሆን ልዩነቶቻችን በማጥበብ፤ ጠብታዎች ባህር እዲሆኑ ማድረግ ነው። መፍትሔው እጅን አጣምሮ ጥቂቶች ታምር እንዲሰሩ መጠበቅም አይደለም። መፍትሔው ከያንዳንዳችን የሚጠበቀውን ሌላውን ሳንጠበቅ መወጣት እንጂ። ስለዚህ አምባገነኖችን መካብ ዙፋናቸውን አግዝፎ በመመልከት ከትግል መሸሽ የችግሩ መፍትሔ በጭራሽ ስለማይሆን ኑ! ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አገዛዙን ከህዝብ ጫንቃ ለማውረድና ሃገርን ለማዳን እያደረገ ያለውን ትግል ይቀላቀሉ በማለት ሃገራዊ ጥሪውን በድጋሚ ያቀርባል።

ከወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የእስርና እንግልት ማብራሪ

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራና ድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ በደቡብ ቀጠና በወላይታ ዞንና በሲዳማ ዞን አዋሳ ከተማ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የፓርቲውን የትግል ስትራቴጅክ ዕቅዶች ላይ ማብራሪያ፣ ደንብና ፕሮግራም ለመስጠት እንዲሁም የስራ ጉብኝት ለማድረግ በ 12/07/06 ወደ ወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ተገኝተው ነበር፡፡ በ13/07/06 ደግሞ ከሶዶ ከተማ ስራ አስፈፃሚና ከወረዳ አመራር አባላት ጋር የፓርቲያችንን ደንብ፣ ፕሮግራምና ቀጣይ የስራ አቅጣጫ አስመልክቶ የተሰናዳው ውይይት ላይ ለመታደም ከ32 በላይ አመራሮችም ተገኝተው ነበር፡፡

ቅዳሜ በ 13/07/06 ዓ.ም ከአባላት ጋር ባለው ዕቅድ መሰረት የፓርቲያችንን ህጋዊ ሰነዶችን ለወረዳና ለዞን አመራሮች ለመስጠት፣ ቀጣዩን ሀገራቀፍ ምርጫ አስመልክቶ መረጃ ለመለዋወጥ ምርጫችን የነበረው የፓርቲያችን አባል የሆነውና ወጣ ብሎ ፀጥታ የሰፈነበት ግቢ ነበር፡፡ ይህንን ለማድረግ ህገ መንግስታዊ መብት ነበረን፡፡ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የፖለቲካ ደንብና ፕሮግራማቸውን ለዞንና ለወረዳ አመራሮች ለማስጨበጥ ፈቃድ እንደማያስፈልግ ጠንቅቀን እናውቅም ነበር፡፡
በተለይም ሃለማሪያም ደሳለኝ በሞግዚትነት ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ወላይታ ሶዶ ነፃነት አልባ ከተማ እንደሆነች ለማረጋገጥ ችለናል፡፡ ወላይታ በካድሬ ተወጥራለች፡፡ ዝርዝሩን በቀጣይ እንደምናቀርብ ቃል እየገባን ለአሁን በእኛ ላይ የደረሰውን በቅንጭቡ እንደሚከተለው ለኢትዮጵያ ህዝብና ለታሪክ እናቀርባለን፡፡
1. 32 የሚሆኑ አንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራሮች የተሰባሰቡት ከላይ በገለፅነው አላማና ህገ መንግስታዊ መብታችንን ተጠቅመን ቢሆንም ለውይይት ቅድመ ዝግጅት ስናደርግና ውይይቱን ለመጀመር ስንዘጋጅ መታወቂያ የሌላቸው ከ 8-10 የሚሆኑ ጡንቻቸው የፈረጠመ ግለሰቦች እንደ ኮማንዶ ለውይይት የተገናኝበትን የአባላችንን ጊቢ ሰብረው በመግባት የያዝናቸውን የፓርቲ ሰነዶች፣ ሳምሰንግ ጋላክሲ ስልኮችና ያገኙትን ሁሉ ዘርፈው ሂደዋል፤ አመራሮችን ደብድበዋል፡፡
2. እነዚሁ ደብዳቢዎች ታርጋ ቁጥር በሌላቸው ሞተሮች በመታጀብ ፖሊስ ይዘው በመምጣት ፕሮግራማችንን ለማደናቀፍ በሃይልና በጉልበት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደውናል፡፡
3. ፖሊስ ጣቢያውም እኛን የደበደቡንንና ንብረታችንን የቀሙንን ሲቢል ለባሽ ካድሬዎች በመልቀቅ የአንድነት ፓርቲ 20 አመራሮችን የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሻለቃ ላሊሼ ኦሌ ቢሯቸው አስገብተው ችግሩን እንደሚቀርፍ አመራር ካነጋገሩንና ቃላችንን ከተቀበሉ በኋላ ሞባይሎቻችንን በመንጠቅ እንድንታሰር አድርገዋል፡፡
4. የእስሩ ሰዓት ከቀኑ 5፡00 ጀምሮ ነው፡፡ እንድ ቀፋፊና አስቀያሚ ማጎሪያ ውስጥ ካስቀመጡን በኋላ ከምሽቱ 2፡00 ላይ ህገወጥ ስብሰባ አድርጋችኋል በማለት ቃል ስጡ የሚል ምዝገባና ህገ ወጥ ስብሰባ እንዳደረግን እንድንመሰክር ለማስገደድ ቢሞክሩም እኛ መብታችንን እንደተጠቀምን እንጂ እነሱ እንደተረጎሙት ህገ ወጥ ስብሰባ እንዳላደረግን ሀቁን ስንነግራቸው እንዲሁም ሀሰትን ከመቀበል መታሰር እንደሚቻል የአንድነት አባላት ቁርጠኛ እንደሆንን ሲያውቁ ግራ ተጋብተው የበላይ አካል እስከሚያረጋግጥላቸው ጠብቀው ከእኩለ ለሊት በኋላ (ከምሽቱ 6፡30) በኋላ በእስር ላይ የቆዩ ከ20 በላይ ከፍተኛ አመራሮች እንዲወጡ ተደርጓል፡፡ ይሄ የሆነው ለመፍታት ታስቦ ሳይሆን ከወረዳ የመጡ አባላት ማደሪያ ቦታ እንዲያጡና ለአደጋ እንዲጋለጡ በማሰብ ነው፡፡

Saturday, March 22, 2014

“ውሃ፣ መብራት፣ ኔትዎርክ የለም ፤ ኑሮ ከበደን” ሰሚ ጆሮ ያጣ የሕዝብ እሮሮ


“ውሃ የለም፤ መብራት፤ ኔትዎርክ የለም፤ መብት የለም፤ ፍትህ የለም፤ ኑሮ ከበደን” እያሉ ስለኑሮዓቸው የተሰማቸውን በሀቅ የተናገሩ ልጃገረዶች በጋጠወጥ የህወሓት ካድሬዎችና ታጣቂዎች እጅ መከራና ስቃይ እየደረሰባቸው ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ በእነዚህ ለጋ ወጣቶች ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ በዝምታ ያልፋል ተብሎ አይታመንም።
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮን ጨምሮ በወያኔና የጥቅም ተጋሪዎቹ ሥር የሚተዳደሩ መገናኛ ብዙሃን በየዕለቱ ያለማቋረጥ ከሚዘገቡት የልማትና የዕድገት ዘገባዎች ከፍተኛውን ስፍራ የሚይዘው በአገራችን ውስጥ እየተሠሩ ስላሉ ትላልቅ የሃይድሮ ኤለክትሪክ ማመንጫ ግንባታዎች፤ በየከተማው ስለተዘረጉ የውሃ መስመሮች፤ የስልክ አገልግሎት ለማዳረስ ስለተወሰዱ እርምጃዎች፤ ስለ ረጃጅም የባቡር መስመሮች ግንባታ እና ስለ አገር አቋራጭ የመንገድ ሥራዎች የሚቀርቡ የተጋነኑ ዘገባዎች ናቸው።
እነዚህ የልማት አውታሮች ግንባታ በአብዛኛው የሚካሄዱት ከምዕራባዊያን መንግሥታት በሚሰጡ የገንዘብ እርዳታና ዕዳው ለልጅ ልጆቻችን በሚተርፍ አለም አቀፍ የገንዘብ አበዳሪ ድርጅቶች ወለድ እያስከፈሉ በሚሰጡት የረጅም ጊዜ ክፍያ ብድር እንደሆነ ግልጽ ነው።
ወያኔ ሥልጣን ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 23 አመታት በድህነት ቅነሳና የልማት ማስፋፊያ ስም ከአለም አቀፍ ኅብረተሰብ የተቀበለው የገንዘብ መጠን ሲሰላ ኢትዮጵያ አገራችን እንደ አገር ከተመሰረተችበት ዘመን ጀምሮ በብድርም ሆነ በእርዳታ ስም ይህንን ያህል መጠን ገንዘብ አግኝታ እንደማታውቅ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይናገራሉ ። በዚህም መሠረት ገንዘቡ በአግባብ ሥራ ላይ ውሎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ አገራችን የትና የት በደርሰች ነበር እያሉ የሚቆጩ የአገሪቱ ልሂቃንና ቅን አሳቢ ዜጎች ቁጥር ቀላል አይደለም ።
የተባበሩት መንግሥታት የልማት ድርጅት ከ3 አመት ገደማ በፊት ይፋ ባደረገው አንድ መረጃ ወያኔ ሥልጣን በተቆጣጠረባቸው የመጀመሪያዎቹ 9 አመታት ብቻ ከ11.5 (አሥራ አንድ ነጥብ አምስት ) ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በህገወጥ መንገድ ከአገር አሽሽቶ በምዕራባዊያን አገሮች ባንኮች ደብቆአል ። ይህ ከደሃው ጉሮሮ ተቀምቶ በባለሥልጣናቱ የተዘረፈና በህገወጥ መንገድ ከአገር የሸሸው 11.5 ቢሊዮን ዶላር በትክክል ልማት ላይ ውሎ ቢሆን ኖሮ ወያኔዎች “ባለ ራዕዩ መሪያቸን” በሚሉት ዘረኛው መለስ ዜናዊ ሥም ለመሰየም ደፋ ቀና የሚሉትን ጅምር “የህዳሴ ግድብ” አይነቱን ሁለት ግዙፍ ግድቦችን በመገንባት የአገሪቷን ገጽታ አበላሽቶ የኖረውን ረሃብ ከምንጩ ማጥፋት ይቻል ነበር።

Friday, March 21, 2014

ለነፃነት የምናደርገው ትግል በህገ ወጥ እስርና ማስፈራሪያ አይደናቀፍም! (በሰማያዊ ፓርቲ)

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

“ማርች-8″ የሴቶችን ነጻነትና እኩልነት እንዲሁም ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚከበር የሴቶች ቀን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህን በዓል አስመልክቶ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ባለፈው ዕሁድ የካቲት 30/2006 ዓ.ም ሴቶች ብቻ የሚሳተፉበት የጎዳና ላይ ሩጫ ማዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡ በዚህ የሐገራችንም ሆነ የዓለም ሴቶች የነጻነት ቀናቸውን በሚያከብሩበት ዕለት እንደሌሎች ሴቶች ሁሉ የሰማያዊ ፓርቲ አአባላትም አላማውን ደግፈው በዕለቱ ቀኑን አስመልክቶ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ በዚህ በሴቶች የነጻነት ቀን በስርዓቱ ላይ የሚነሱ ብሶቶችን ካሰሙት ተሳታፊዎች ውስጥ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሚገኙበት ሲሆን፣ በተለየ መልኩ በእነዚህ አባላቶቻችን ላይ ያነጣጠረ የአፈሳ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንደዚህ አይነት ህዝባዊ መድረኮችን ላይ ብቻ ሳይሆን ሁሌም ህዝብ ላይ የሚደርሰው በደል በማጋለጥ መብት እና ለአገራችን ብሄራዊ ጥቅም በመቆም በገዥው ፓርቲ ተደጋጋሚ ህገ ወጥ እርምጃ ሲወሰድበት ቆይቷል፡፡ የተደረገው ህገ ወጥ ድርጊት ከዚሁ ፓርቲው ለህዝብና ለአገር መቆሙን ተከትሎ እየደረሰበት ያለው የከፋ የጭቆና አካል ነው፡፡Semayawi party press conference, Addis Ababa
ህገ ወጥ ድርጊቱን የበለጠ አስገራሚ የሚያደርገውም አባላቶቻችን የታሰሩበት ምክንያት “የጣይቱ ልጅ ነን” ፣ ህወሓት/ኢህአዴግን ምን ያህል ከታሪክ ጋር የተጣላ መሆኑን ከማሳየቱም በተጨማሪ አባላቶቻችን ለማስር እንግልት ወቅት በአባላቶቻችን ላይ የደህንነት አካላት ነን በሚሉ ግለሰቦች ማስፈራሪያና ዛቻ ተፈፅሞባቸው፡፡ አንዳንዶቹ አባላቶቻችን በሌሊት ጭምር ከእስር ክፍላቸው ወጥተው ቃል እንዲሰጡ ተከልክለዋል፡፡ ሙከራ ተደርጎባቸዋል፡፡ ከጠያቂ ቤተሰቦቻቸውና የትግል ጓደኞቻቸው ጋር እንዳይገናኙ ተከልክለዋል፡፡ የተጠረጠሩበት ክስ የማያስከስስና በነፃ የሚያስለቅቃቸው መሆኑ በየካ ክፍለ ከተማ ፍትህ ፅ/ቤት አቃቤ ህጎች ከተገለፀላቸው በኋላም በድጋሚ ፍርድ ቤት በማቅረብ እያንዳንዳቸው 1300 ብርና የመታወቂያ ዋስ በዋስትና እንዲቀርቡ ተጠይቀዋል፡፡

Tuesday, March 18, 2014

የቁልቁለት መንገድ! – ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ




… በማስመሰል ታጥሮ መሆን በጠፋበት
ምን አገባኝ የሚል በተከማቸበት
የባይተዋር መንፈስ ከሞላ ባገሩ
ዘመኑን ማወቂያ ይሄ ነው ሚስጥሩ
ይሄን ጊዜ ጠርጥር እንደጠፋ ዘሩ፡፡                                          
(ገጣሚ ደምሰው መርሻ/ያልታተመ)

አዎን፣ ገጣሚ ደምሰው እንዳለው እኔም በዚህ ዘመን “ዘሩ እንደጠፋ” አሊያም ሊጠፋ እንደተቃረበ እጠረጥራለሁ፡፡

ስለምን? ቢሉ …በኢትዮጵያችን ለህሊናው፣ ለሕዝብና ለሀገሩ የሚቆረቆር፣ የእውነት ተሟጋችና የሞራል ልዕልናን የተቀዳጀ ሙሉ ሰው ፈልጎ ማግኘት እጅግ አተካች ሆኗልና፡፡ የግል ጥቅም አሳዳጅ፣ አፋሽ-አጎንባሽ በሞላበት፣ እንደ ቴዎድሮስ ለሀገር ቤዛ መሆን፤ እንደ ግርማሜዎቹ እና ወርቅነህ የራስን ምቾት ወዲያ ጥሎ በጠገበ ሆድ    ከወገን ጋር መራብና ከጎኑ መቆም፤ እንደ አቶ ሽፈራው ደሳለኝ አስፈሪ ሞት ከከበበው ሸለቆ ውስጥ በህይወት ለመውጣት ሲባል የጠላትን ጫማ ከመላስና ያላመኑበትን ተናግሮ ምህረት ከመጠየቅ ይልቅ በድፍረት ሞትን ፊት ለፊት መጋፈጥ ወይም ግንባርን ለአረር መስጠት እንደ ተረታ-ተረት ከተቆጠረ ዘመናት አልፏል (አቶ ሽፈራው ደሳለኝ ማን ናቸው? ለሚለኝ አንባቢዬ ‹‹የታኀሣሡ ግርግር እና መዘዙ›› የተሰኘውን የብርሃኑ አስረስ መጽሐፍ ገፅ 302ን እንዲያነብ እጋብዘዋለሁ) አሊያም ደግሞ የሰው ዘር በመሆን ብቻ የሚገኘውን የሞራል ልዕልና ከትውልድና ሀገር ጥቅም አኳያ ለማጠየቅ በዚህ አውድ ለማነሳው ተጠየቅ በአንፅሮ ለማፍታታት ይጠቅመኝ ዘንድ እኔው ራሴ እዚሁ ጠቅሼው አልፋለሁ፡፡

የመጽሐፉ ደራሲ ‹‹በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጊዜ የድጋፍ ንግግር አድርጋችኋል በማለት በመንግስት ተይዘው ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ከተላኩት አንዱ የሆኑት…›› ብለው ከአቶ ሽፈራው ደሳለኝ ጋር ከአስተዋወቁን በኋላ እንዲህ በማለት ትርክታቸውን ይቀጥላሉ፡- ‹‹…አቶ ሽፈራው ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ተልከው ለፖሊስ ቃላቸውን ሰጥተው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ የእምነት ክህደት ቃል ሲጠየቁ ዳኛው ‹ሠርተሃል ለተባለው ወንጀል ጥፋተኛ ነህ፣ አይደለህም?› ይላቸዋል፡፡ ‹የቱን ወንጀል?› ሲሉ አቶ ሽፈራው ዳኛውን ይጠይቃሉ፡፡ ዳኛው አቶ ሽፈራው ሠርተዋል የተባለውን የወንጀል ቃል ሊናገሩት አልወደዱም አልደፈሩምምና ‹አንተ የሠራኸውን?› ብለው ጠየቁ፡፡ አቶ ሽፈራው ‹እስቲ ወንጀል የተባለው ይነበብልኝ› ብለው አጥብቀው ይጠይቃሉ፡፡ ይሄን ጊዜ ዳኛው ሳይወዱ ‹ይህን ጣሳ እግዚአብሔር ገላገለን፣ አወረደልን ማለትህን፤ …ለዚህ ጥፋተኛ ነህ አይደለህም?› ይሏቸዋል፡፡ ‹የለም ተስተካክሎ ይጻፍልኝና እምነት ክህደቴን ልናገር› ይላሉ፡፡ ‹የለም በዚህ ላይ ጥፋተኛ ነኝ በል› ይሏቸዋል፡፡ ‹ትክክለኛ ቃሌ ይጻፍና ነው እንጂ እንዲሁ ጥፋተኛ ነኝ፤ አይደለሁም፤ አልልም› ብለው ይመልሳሉ፡፡ ‹እሺ ምን ተብሎ ይስተካከል› ሲሏቸው፤ ‹ይህን የበሰበሰ የተጠረማመሰ አሮጌ ጣሳ እግዚአብሔር ገላገለን ነው ያልኩት› ሲሉ ዳኞቹ የተባለውን አልሰማንም ለማለት ራሳቸውን ጠረጴዛ ስር አግብተው ተደበቁ፡፡››

የኦህዴድ አባላት በአቶ አለማየሁ ሞት ጉዳይ ጥያቄ እያቀረቡ ነው


 ኢሳት ዜና :-የኦሮሚያ ክልል እና የኦህዴድ ፕሬዚዳንት የነበሩትና ሰሞኑን ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የአቶ አለማየሁ አቶምሳ የሞት መንስኤ እንዲጣራ የኦህዴድ መካከለኛና ዝቅተኛ ካድሬዎችና አባላት በየመድረኩ ጥያቄ እያነሱ መሆኑ ከፍተኛ አመራሩን ጭንቀት ውስጥ እንደጣለው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጹ፡፡

አቶ አለማየሁ ለሞታቸው መንስኤ የሆነው ከምግብ ጋር የተሰጣቸው መርዝ ነው የሚሉ መረጃዎች ኢሳትን ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ይፋ መሆኑን ተከትሎ አብዛኛዎቹ መካከለኛና ዝቅተኛ የድርጅቱ አባላትና ካድሬዎች የአቶ አለማየሁ ሞት በገለልተኛ ወገን ተጣርቶ እንዲቀርብ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ጥያቄ ማቅረብ ጀምረዋል፡፡
በተለይ ከአቶ አለማየሁ ሞት ጀርባ የቀድሞ የኦሮሚያ ፕሬዚደንት አቶ አባዱላ ገመዳ እጅ አለበት መባሉና ጉዳዩም ሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነትን ጠራርጎ ለማጽዳት አቶ አለማየሁ የጀመሩት እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ ሆን ተብሎ የተፈጸመ ነው በሚል መገለጹ አብዛኛውን የድርጅቱን አባላት ቁጭት ውስጥ ጥሏል፡፡

በዚህም ምክንያት አቶ አለማየሁ የጀመሩትን የኪራይ ሰብሳቢነትና የሙስና ትግል አጠናክረን እንቀጥላለን የሚሉ መፈክሮች በየወረዳውና በየቀበሌው በስፋት በመስተጋባት ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡
አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ላቸው የኦህዴድ አባል ለዘጋቢያችን እንደገለጹት የአቶ አለማየሁ ሞት እንዲጣራ ጣያቄ ሲቀርብ ከፍተኛ አመራሩ ይሄ የጸረ ሰላም ሃይሎች አሉባልታ ነው በሚል ምላሽ ለመስጠትና ለማጣጣል ሙከራ እንደሚያደርጉ አስታውሰው የሁሉን አመኔታ ለማግኘት ግን ፍረጃ ውስጥ ከመግባት ይልቅ ነገሩን በገለልተኛ ወገን ማጣራቱ ይቀል ነበር በማለት ነቀፌታውን አጣጥለውታል፡፡

በኑሮ ዉድነት ላይ በአዲስ አበባ የአንድነት ምክር ቤት ሰልፍ ሊጠራ ነው !

የአንድት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ስራ አስፈፃሚ የተቃውሞ ሰልፍ ሊጠራ ነው እንደሆነ የፍኖት ጋዜጣ ዘገበ። «በአዲስ አበባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣውን የውሃ፣የመብራትና የቴሌኮም አገልግሎት ጥራት መጓደልና የአገልግሎት መቋረጥ መንግስት በአፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ለመጠየቅ፣ የከተማዋን ነዋሪዎች በማነቃነቅ ደማቅ የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የአንድት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ስራ አስፈፃሚ መወሰኑን የዞኑ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ» ሲል ነው ፍኖት የዘገበው።


ይህ የአንድነት ፓርቲ አዲስ አበባ ምክር ቤት የሚጠራዉ ሰልፍ፣ የአንድነት ፓርቲ ይፋ ካደረገው የአሥራ አራት ከተሞች የሚሊየንም እንቅስቃሴ የተለየና በተጨማሪ የሚደረግ ሲሆን፣ የሚሊየነም እንቅስቃሴ በመሬት ባለቤትነትና በፍትህ ላይ ያተኮረ እንደሆነ በስፋት የተዘገበ ነው።

የአዲስ አባበ የአንድነት ምክር ቤት፣ በሃያ ሶስቱም የአዲስ አበባ ወረዳዎች መቃቅር ያለው ሲሆን፣ ከማእከላዊ ፓርቲ ዉጭ፣ በራሱ በርካታ እንቅስቃሴዎች የሚያደርግ ምክር ቤት እንደሆነ ይታወቃል። ፓርቲዉ አባላትን በአዲስ አበባ እንዳደረጉት በራሳቸው አነሳሽነት ሰላማዊን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንዲያደርጉ የሚያበረታታ እንደሆነ ብዙ ጊዜ አመራር አባላቱ ሲናገሩ ተሰምተዋል።

Sunday, March 16, 2014

ኢህአዴግ ሰልፍ የማይጠራን እኮ ኑሮአችንን ሰልፍ ስላደረገው ነው!


የታክሲ—የዳቦ—የውሃ—የግብር—የቦሎ—ረዣዥም ሠልፎች—-
  • የማሌዢያው አውሮፕላን ኢትዮጵያ ውስጥ አልወደቀም ተባለ!
  • “መሬት የግል ይሁን” የዘመኑ “መሬት ላራሹ” ነው እንዴ?
እኔ የምላችሁ … “አንድነት” ፓርቲ ባለፈው ሳምንት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የተሰኘውን ቁጥር 2 ንቅናቄ መጀመሩን ሰምታችሁልኛል?! አይዟችሁ … ብትሰሙም ችግር የለውም፡፡ ይሄኛው “ሽብር” ምናምን የሚል ነገር የለውም (“መሬት የግል ይሁን” ማለት ሽብር ነው እንዴ?) እናላችሁ … የአሁኑ አጀንዳዬ መሬት ነው ብሏል፤ ፓርቲው፡፡ አዎ! መሬት የግል ይሁን እያለ ነው- አንድነት፡፡ (ማን ነበር “ድርሻዬን” እያለ ያቀነቀነው?) እንደምታውቁት … ባለፈው ዓመት ፓርቲው ያደረገው ንቅናቄ፣ ለእኔ ቢጤ “አንድ ለእናቱ” ትንሽ ያስቦካ ነበር፡፡ በሚሊዮኖች ድምፅ “የፀረ-ሽብር አዋጁን አሰርዛለሁ” አይደል ያለው፤ አንድነት፡፡ ኢህአዴግ ያኔ በልቡ “On my dead body!” (ሞቻታለኋ!) ያለ አይመስላችሁም?
እውነት ግን ፓርቲው 1ሚ. ፊርማ አሰባስቧል ማለት ነው? ለነገሩ አንድነት ፓርቲ 1ሚ. ደጋፊ ያጣል ማለት ዘበት ነው፡፡ ፓርቲው ምንም አልተንቀሳቀሰም ቢባል እንኳ ኢህአዴግ አለለት! ከምሬ እኮ ነው … አውራው ፓርቲ በየሰበቡ የሚያስቀይማቸው ሰዎች፤ አንድም ባህርማዶ አሊያም እንደ አንድነት ያሉ ተቃዋሚዎችን መቀላቀላቸው አይቀርም (ጠላት በማብዛት ኢህአዴግ አቻ የለውም!) እኔ የምላችሁ … የኢህአዴግ አባላት ቁጥር ስንት ሆነ?  ወይስ እንደ ኢኮኖሚ ዕድገቱ አሁንም እየገሰገሰ ነው፡፡ በነገራችሁ ላይ … ኢትዮጵያ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገራት ተርታ የምትሰለፍበት ጊዜ ትንሽ ቀረብ ሳይል አይቀርም (30 እና 40 ዓመት አይፈጅም ማለቴ ነው!) አንድ ወዳጄ ደስ ይለዋል ብዬ ይሄን የምስራች ብነግረው ምን እንዳለኝ ታውቃላችሁ? “እሰይ፤ ኢህአዴግ ተጨማሪ 30 እና 40 ዓመት ስልጣን አያስፈልገውም!” ብሎኝ ቁጭ አለ! እውነቱን ልንገራችሁ አይደል … ስለ ስልጣን ቀን ተሌት የሚያስበው ሥልጣን ላይ የተቀመጠ  ብቻ ነበር የሚመስለኝ፡፡ ለካስ እንደ እኔ ወዳጅ ያለውም ስለ ስልጣን ያስባል፡፡ (“ወንበሩ እንደሆነ አንድ ነው” ያሉት የቀድሞው መሪ ትዝ አሉኝ!)

በሕወሓት ጄኔራሎች እና በብኣዴን የጦር መኮንኖች መካከል ውጥረት ነግሷል::


ህገመንግስታዊ ጥያቄ ባነሱ ከጄኔራልነት እስከ ሻምበልነት ማእረግ ባላቸው የቀድሞው የኢሕዴን ታጋዮች እና የአሁን የብኣዴን የጦር መኮንኖች እና በሕወሃት ጄኔራሎች መካከል ከፍተኛ የሆነ የመብት ጥያቄዎችን ያማከለ እና ህገመንግስታዊ ስርኣትን ተከትሏል የተባለለት ጥያቄዎችን ተከትሎ ከፍተኛ ውጥረት መከሰቱን የመከላከያ ምንጮቻችን ጠቁመዋል::
ባለፉት ሰሞናት የተደረጉት ስብሰባዎች በከፍተኛ አለመግባባት የተበተኑ ሲሆን በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ በስፋት የፓርቲ ስራዎች እንጂ ሃገራዊ ስራዎች እየተሰሩ አይደለም የሚሉ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊቱ ለህገመንግስቱ መከበር ተገኢ መሆን አለበት በአሁን ወቅት ለአንድ የፓርቲ አመራር እና ለፕሮፓጋንዳ ተገኢ ሆነናል የሚሉ ተመሳሳይ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በሰራዊቱ ውስጥ ያለውን የእድገት የትምህርት እና የደምወዝ መብትን በተመለከተም ከፍተኛ ክርከር ቢደረግም ካለመግባባት መኮንኖቹ ጥርስ እንደተነካከሱ ወደየመጡበት ተበታትነዋል::
የሰራዊት አባላትን ለመቀነስ በተደረገው ጥናት መሰረት ለምን ሁለት ብሄር ላይ አተኮረ የሚሉ ጥያቄ እንዲሁም የስኮላርሺፕ አድሏዊነት በተመለከተ ጠንከር ያሉ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን እንዲሁም ከአንድ ብሄር ለትምህርት ተመርጠው የሚላኩ መኮንኖች በዛው ሳይመለሱ ይቀሩና ነገሩ ይድበሰበሳል የሚሉ አስጨናቂ ጥያቄዎች ተከታትለው ቢነሱም ከመድረኩ መልስ ሳይሰጥባቸው ተድበስብሰው አልፈዋል::ከአንድ ብሄር ብቻ ተመርጠው ለትምሕርት አውሮፓና አሜሪካ ከሄዱት መኮንኖች 80 ከመቶ ያልተመለሱ ሲሆን ይህ ጉዳይ ተድበስብሶ ሌላው ብሄር ስኮላሺፕ እንዳያገኝ ምክንያት እየተፈጠር በዚያው ስለምትከዱ ሃገር ውስጥ በቂ አካዳሚ ስላለ እዚህ እንድንማር ይደረጋል::ስኮላሺፕ የሚሰጣቸው ለማይመለሱ መኮንኖች ነው የሚሉ አቤቱታዎች ተሰምተዋል::
በሕወሓት ጄኔራሎች እና በብኣዴን ከፍተኛ የጦር መኮንኖች መካከል የተነሳውን ፍጥጫ ተከትሎ ጄኔራል አበባውን ወደ ሲችል ባለስልጣንነት ለማዘዋወር የታቀደ መሆኑን የገለጹት ምንጮሽች በአሁን ሰአት ጄኔራሉ እንደ ቁም እስረኛ አብዛኛው ጊዜያቸውን በመኖሪያ ቤታቸው እንደሚያሳልፉ እና ወደ ቢሯቸው አልፎ አልፎ እንደሚገቡ ታውቋል::

Saturday, March 15, 2014

መልካም ዜና የአንድነትና የመኢአድ ውህደት ወደሚታይ ምዕራፍ ተሸጋገረ


መልካም ዜና
የአንድነትና የመኢአድ ውህደት ወደሚታይ ምዕራፍ ተሸጋገረ
የአንድነትና የመኢአድ ብሄራዊ ምክር ቤቶች በውህደት ዙሪያ የፊታችን እሁድ ሊወያዩ ነው፡፡ፓርቲዎቹ እንዲዋሃዱ ይሁንታን የሰጡት የፓርቲዎቹ ብሄራዊ ምክር ቤቶች የውህደቱን ሂደት ሲመሩ በቆዩት ሽማግሌዎች አማካኝነት የፊታችን እሁድ ውይይት እንደሚያደርጉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ሰንደቅ ጋዜጣ መኢአድ አንድነትን በውህደት መዘግየት እንደከሰሰ በመጥቀስ ባሳለፍነው ረቡዕ ዘግቦ የነበረ ቢሆንም ፓርቲዎቹ ለመዋሃድ በጀመሩት ሂደት በመቀጠል በጣም በቅርቡ ትግላቸውን በአንድ ፓርቲ ጥላ ስር በማድረግ ህዝብን እንደሚያደራጁ ብሄራዊ ምክር ቤቶቹ ለውይይት ለመቀመጥ ቀጠሮ መያዛቸውን እንደ መነሻነት በመጥቀስ መተንበይ ይቻላል ፡፡

የኢህአዴግ ማመልክቻ ድጋሚ ውድቅ መደረግ አለበት!


በመጀመሪያ አፋኝ ሕጎች መሠረዝ አለባቸው!
የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) ለተሰኘ ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ በድጋሚ ያቀረበው የእውቅና ጥያቄ ማመልከቻ ውድቅ መደረግ እንዳለበት ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት (Human Rights Watch) ድርጅት አስታወቀ፡፡ ኢህአዴግ የእውቅና ማመልከቻ አስገብቶ ውድቅ ተደርጎበት የነበረ ሲሆን በኢትዮጵያ ላይ የታወጁት አፋኝ ሕጎች እስካልተወገዱ ድረስ ድጋሚ ማመልከቻው ውድቅ ሊደረግ እንደሚገባው ጨምሮ ተነግሯል፡፡
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከሳምንታት በፊት “
ክሌር ሾርት
ዛሬ የወጣው የሰብዓዊ መብት ድርጅት መግለጫ ይህንኑ የኢህአዴግን ጥያቄ የሚያስረዳ ሲሆን በአፋኝ ህጎቹ ላይ አንዳችም ለውጥ ያላሳየው ኢህአዴግ ማመልከቻው ውድቅ መደረግ እንዳለበት መግለጫው በአጽዕኖት ይናገራል፡፡ ምክንያቱንም ሲጠቅስ “የኢትዮጵያ መንግሥት ሚዲያውን አፍኗል፤ (ሰብዓዊ መብት እንዲከበር) እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሁሉ አድቅቋል” በማለት ያስረዳል፡፡ ኢህአዴግ ከዚህ በፊት ባስገባው ማመልከቻ ላይ የEITI ቦርድ ውሳኔውን ሲያስተላልፍ “የመያዶች ሕግ የተሰኘው አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆን እስካልተደረገ” ማመልከቻው ሊታይ እንደማይገባው በዋንኛነት ማመልከቻው ውድቅ እንዲደረግ የተደረገበት ምክንያት እንደነበር የጠቀሰው የሰብዓዊ መብት ድርጅት መግለጫ EITI አሁንም ይህንኑ ውሳኔውን እንዲያከብር ጠይቋል፡፡

Friday, March 14, 2014

በኢትዮጵያ የሚደረጉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዛሬ እለት ጄኔቭ ስዊትዘርላንድ ውስጥ በዝርዝር ለውይይት ቀረበ


በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ ውይይት ጄኔቭ ስዊትዘርላንድ ውስጥ ዛሬ ተካሂዷል ። የተለያዩ ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ባዘጋጁት በዚሁ ውይይት ላይ በኢትዮጵያ ይፈፀማሉ የተባሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዝርዝር ቀርበዋል።
Karte Äthiopien englisch
መንግሥት የሰብዓዊ መብት አያያዙን እንዲያሻሽል ያግዛሉ የተባሉ ሃሳቦችም ተሰንዝረዋል ። በስበሰባው ላይ የተካፈሉት የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮች ለተሰነዘሩት ወቀሳዎች የበኩላቸውን መልስ መስጠታቸው ተገልጿል ። በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ያተኮረው ውይይት ዛሬ የተደረገው ከ25,ተኛው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጉባኤ ጎን ለጎን ነው ። የውይይቱ ዓላማም በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ ዝርዝር ዘገባ ለተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በመጪው ግንቦት ከመቅረቡ አስቀድሞ ስለሃገሪቱ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው ። ስበስባውን ካዘጋጁት ዓለምዓቀፍ ድርጅቶች አንዱ መቀመጫውን ጆሃንስበርግ ደቡብ አፍሪቃ ያደረገው ሲቪኩስ የተባለው ድርጅት የፖሊሲና የጥብቅና ጉዳዮች መኮንን ቶር ሆድንፌልድ ስብሰባው በተለይ በሶስት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መወያየቱን ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።

በአሜሪካ የሚኖረው የሕወሐት ወንጀለኛ


Bisrat Amare former head of TPLF Intelligence
የሕወሐት አባል የሆነውና በአሜሪካ የሚኖረው ብስራት አማረ በርካታ ወንጀሎችን እንደፈፀመ የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። ሕወሐት በረሃ እያለ የባዶ 6 እስር ቤት ዋና ሃላፊ የነበረው ብስራት አማረ የኢ.ህ.አ.ፓ አባላት የነበሩት እነ ፀጋዬ ገ/መድህን (ደብተራው) ጨምሮ በሕወሐት የተያዙትን በሙሉ ወረኢ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በነበረ እስር ቤት በጅምላ አሰቃይቶ እንደገደላቸው ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ ሰዎች « ኢዲዩና ፊውዳል..» በሚል ባዶ 6 ተብሎ ይጠራ በነበረው እስር ቤት ተሰቃይተው እንዲገደሉ የተደረጉት በብስራት አማረ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮቹ ከዚህ በተጨማሪ የድርጅቱን በርካታ አባላት እንዳስገደለ አያይዘው ገልፀዋል። እነተክሉ ሃዋዝ በዚህ ወንጀለኛ ከተገደሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ያክላሉ። በ1983ዓ.ም ሕወሐት/ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ የሟቹ የደህንነት ሹም ክንፈ ገ/መድህን ምክትል የነበረው ብስራት አማረ ከቤተ መንግስት የጃንሆይ የነበረ ከፍተኛ ወርቅ በመዝረፍ መውሰዱን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚህ የዘረፋ ወንጀል ሆለታ እስር ቤት እንዲገባ መደረጉን ያመለክታሉ። በነስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ትእዛዝ እንዲፈታ ተደርጐ ወደ አሜሪካ የተሸኘው ብስራት አሜሪካ ሲጓዝ የዘረፈውን ወርቅ ይዞ እንደነበረ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ምንጮች በግርምት ይገልፃሉ። ብስራት አማረ አሜሪካ ከመጣ በኋላ ቅርስ የሆኑትንና የዘረፋቸውን ወርቆች መሸጡንና አንዲት ሴት ለማሻሻጥ የተቀበለችውን 1ኪሎ ወርቅ ከወሰደች በኋላ እንደካደችው ማወቅ ተችሎዋል። ብስራት አማረ ስለዚሁ ጉዳይ ተበሳጭቶ የነገራቸው ምንጮች ማረጋገጫ ይሰጣሉ። የብስራት ታናሽ ወንድም የሆነውና በደህንነት ቢሮ ይሰራ የነበረው ታጋይ ጠስሚ (ጠስሚ -ትርጉሙ ቅቤ ማለት ነው) ከስራው በመልቀቅ የአስመጪና ላኪነት ትልቅ ቢዝነስ መክፈቱን የጠቆሙት ምንጮቹ አክለውም፥ ድርጅቱ የተከፈተው ብስራት አሜሪካ ከገባ በኋላ በላከለት ገንዘብ መሆኑን አስታውቀዋል። (ስለዚሁ ጉዳይ በ1995 ዓ.ም በኢትኦጵ ጋዜጣ መረጃው ይፋ መደረጉና የብስራት ወንድም ቅቤ ኢትኦጵ ቢሮ ድረስ በመምጣት የጋዜጣውን አዘጋጅ በድንጋጤ ተውጦ “የራሴን ቢዝነስ ተቋም ነው፤ እነማን መረጃ እንደሚሰጧችሁ አውቃለሁ። እባካችሁ የእኔንም፣ የወንድሜንም ስም አታንሱ?” በማለት ተማጽኖ አቅርቦ ነበር።) ብስራት አማረ ከሽማግሌው ስብሃት ነጋ ጋር ባለው የጠበቀ ግንኙነት ወደ ኢትዮጵያ ሲመላለስ መቆየቱን ያወሱት ምንጮቹ፣ ወንጀለኛውና ዘራፊው መቀሌ ሄዶ አስገደ ገ/ስላሴን እንደከሰሰ አስታውቀዋል። የደርግ ወንጀለኞች ከአሜሪካ በገዢው ፓርቲ እየተወሰዱ ነገር ግን የኢ.ህ.አ.ፓ አባላትንና ሌሎች ንጹሃን ዜጎችን በጅምላ የፈጀና የአገር ቅርስ የዘረፈ ወንጀለኛ ጠያቂ ማጣቱ አስገራሚ ነው ብለዋል ምንጮቹ። ጠያቂ አካል ካለ በወንጀለኛው ብስራት አማረ ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ መሆናቸውን አክለዋል። ይህን ምስክርነትና ማረጋገጫ ሊሰጡ የሚችሉና በአሜሪካ የሚኖሩ ሶስት የቀድሞ የሕወሐት ሹሞች እንዳሉና የብስራትን ወንጀል ጠንቅቀው የሚያውቁ መኖራቸውን አያይዘው ጠቁመዋል።

Thursday, March 13, 2014

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ግምገማ


በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ ውይይት ጄኔቭ ስዊትዘርላንድ ውስጥ ዛሬ ተካሂዷል ። የተለያዩ ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ባዘጋጁት በዚሁ ውይይት ላይ በኢትዮጵያ ይፈፀማሉ የተባሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዝርዝር ቀርበዋል።
Karte Äthiopien englisch
መንግሥት የሰብዓዊ መብት አያያዙን እንዲያሻሽል ያግዛሉ የተባሉ ሃሳቦችም ተሰንዝረዋል ። በስበሰባው ላይ የተካፈሉት የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮች ለተሰነዘሩት ወቀሳዎች የበኩላቸውን መልስ መስጠታቸው ተገልጿል ።በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ያተኮረው ውይይት ዛሬ የተደረገው ከ25,ተኛው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጉባኤ ጎን ለጎን ነው ። የውይይቱ ዓላማም በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ ዝርዝር ዘገባ ለተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በመጪው ግንቦት ከመቅረቡ አስቀድሞ ስለሃገሪቱ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው ። ስበስባውን ካዘጋጁት ዓለምዓቀፍ ድርጅቶች አንዱ መቀመጫውን ጆሃንስበርግ ደቡብ አፍሪቃ ያደረገው ሲቪኩስ የተባለው ድርጅት የፖሊሲና የጥብቅና ጉዳዮች መኮንን ቶር ሆድንፌልድ ስብሰባው በተለይ በሶስት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መወያየቱን ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።
ከነዚህም እጎአ በ2009 ዓም የወጣው የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራት ህግ አንዱ ነው ። ህጉ ከባድ ተፅዕኖ ማሳደሩና መዘዞቹም በውይይቱ መነሳታቸውን ሆድንፌልድ ገልፀዋል ። « በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብት ለሚታገሉ ድርጅቶች በሚለገሰው ዓለም ዓቀፍ የገንዘብ እርዳታ ላይ በተጣሉትን ገደቦች ላይ ተነጋገግረናል በዚህ ህግ ምክንያት በኢትዮጵያ ዓለም ኦቀፍ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች አይሰሩም ። በርካታ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶችም ከሰብዓዊ መብት ጋር የተገናኙ ሥራዎች ማካሄድ አቁመዋል ወይንም ከነጭራሹ ተዘግተዋል »

በዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን ዝክር፤ በእህቶቻችን ኮርተናል!!!



ለዘንድሮው ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን መታሰቢያ በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገው የሩጫ ትዕይንት ላይ ወጣት ሴቶች ባሳዩት ልበ ሙሉነት ኮርተናል። የሩጫውን ትዕይንት አስታከው፣ በአብዛኛው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እንደሆኑ የተነገረላቸው ወጣት ሴቶች ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለህሊና እስረኞች መፈታት እና ለሀገር አንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድረገው ጮኸዋል፤ ዘምረዋል። እነዚህ ወጣት ሴቶች በሥርዓቱ ምን ያህል እንደተማረሩ በቃላትም በአካል ንቅናቄም አሳይተዋል። ዘረኛውና ፋሽስቱ ወያኔ ግን “ለምን ተቃወማችሁኝ” ብሎ አስሯቸዋል፤ ከፊሎቹም የደረሱበት አይታወቅም። በእህቶቻችን ቆራጥነት ኮርተናል፤ በወያኔ የፈሪ ዱላ ደግሞ ተቆጥተናል። በ1997 እና 98 “የወላጆቻችን ድምጽ ይከበር” ያሉ ሕፃናትን የጨፈጨፈው ወያኔ በ2006 ወጣት ሴቶችን ከማሰቃየት ይመለሳል ብለን አናምንም። ወያኔ እስካልተወገደ ድረስ የፈሪ ዱላው የማይቀር ነገር ነው።
የወንዶቹን ያህል የተዘገበ አይሁን እንጂ በክፉም በደጉም ሴቶች ያልተሳተፉበት የኢትዮጵያ ታሪክ የለም። የቅርብ ጊዜ ታሪካችንን እንኳን ብናይ በፋሽስት ወረራ ወቅት ኢትዮጵያዊያን ሴቶች በአርበኝነት ዘምተው አዋግተዋል፤ ተዋግተዋል። በተለያዩ ምክንያቶች መዝመት ያልቻሉት ደግሞ በውስጥ አርበኝነት ተሰልፈው የጠላት ምስጢሮች ለአርበኞች እንዲደርሱ በማድረግ ከፍተኛ ጀብዱዎችን ፈጽመዋል። ከፋሺስት ወረራ ወዲህ በነበሩ ዓመታት ውስጥም ለፍትህ እና ለነፃነት በተደረጉ ተጋድሎዎች ሴቶች ጉልህ ተሳትፎ ነበራቸው። በተማሪዎች ትግል ውስጥ ለምሳሌ፣ ወጣት ሴቶች በአመራር ደረጃ በመሳተፍ ትግሉን መርተዋል፤ የሕይወት መስዋዕትነት ጭምር ከፍለዋል። ከዚያ ወዲህም በነበሩት ዓመታት በኢሕአፓ እና ሌሎችም ድርጅቶች አመራርና አባልነት ተሳትፈው ከፍተኛ ተጋድሎ ያደረጉ ኢትዮጵያዊያን ሴቶች ነበሩን። በቅርቡም በምርጫ 97 እንቅስቃሴም የሴቶች በተለይም የወጣት ሴቶች ተሳትፎ ምን ያህል ጉልህ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነውና እናስታውሳለን። ለምርጫ ድምጽ መከበር ወጣት ሽብሬ ደሣለኝን ጨምሮ በርካታ ሴቶች ሕይወታቸውን ሰውተዋል፤ ከዚያ የበለጡት ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። ዛሬም እንደ ርዕዮት ዓለሙ የመሳሰሉ ጀግኖች በወያኔ ወህኒ ቤቶች እየማቀቁ፤ በየእለቱ ሰቆቃ (ቶርቸር) እየተፈፀመባቸው መሆናቸው በሀዘንና በቁጭት እናስባቸዋለን።

Wednesday, March 12, 2014

በካፋ ውስጥ እድሜያቸው ለአቅሜ አዳም ባልደረሱ ሴት ልጆቻችን ላይ የጠለፋና አስገድዶ መድፈር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጣ::








በካፋ ውስጥ  እድሜያቸው ለአቅሜ አዳም ባልደረሱ ሴት ልጆቻችን ላይ የጠለፋና አስገድዶ መድፈር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ በማህበረሰቡ ውስጥ ስጋትን ፈጥሮዋል:: ስለሆነም መንግስት በጉዳዩ ላይ ምንም አየነት ትኩረት እየሰጠ ስላልሆነ በተቻለ መጠን የካፋ ተዎላጅ የሆናቹ ሁሉ ይሄን ችግር ለመከላከል እንረባረብ:: እባካችሁ የከፋ ተወላጅ የሆናችሁ እና ኢትዮጵያዊ የሆናችሁ በከፋ ዞን በየ ወረዳ እና ቀበሌ እየተበራከተ የመጣውን  የሴት ልጅ ጠለፋን ለማስቀረት ( ለመቀነስ ) ተነሳሱ። ምንም በማታውቅ ሴት ህፃን ልጅ ትምህርቷን አቋረጣ በገንዘብ እና በደላላ ተደልላ ምንም በማታውቀው ተዳር ለዝያውም ያለ ዕድሜ (ያለ አቻ ጋብቻ ) ስደርስባቸው እንመለከታለን። የሚመለከታቸው አካላት በዞኑ ውስጥ የሚገኙ ወረዳዎች ይህንን ጉዳይ ከመከላከል ምንም ከማያውቀው ማይም ገበሬ ጉቦ በመቀበል ወዴ ሀገር ሽማግለ በመመለስ የታዳጊ ህፃናት ላይ እየነገደ እንደሚገኝ ሁሉም የአከባቢ ህ/ሰብ የሚያውቀው ጉዳይ ሲሆን ይህንን ለመታገል እባካችሁ በያላችሁበት ሆናችሁ በመወያየት ህፃናትን እንታደጋቸው!::

ወያኔ በግንቦት 7 ስም ሠላማዊ ዜጎችን ማሰቃየቱን ባስቸኳይ ማቆም አለበት


Ginbot 7 weekly editorialባለፉት አራትና አምስት አመታት በግልጽ እንዳየነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እኩልነቱን፤ መብቱንና ነጻነቱን ለማስከበር የሚያደርገዉ ትግል ጫና በፈጠረበት ቁጥር ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የራሱን ህገመንግስት የሚደፈጥጡ ህጎች አርቅቆ አያጸደቀ ሠላማዊ ዜጎችን አስሯል፤ ገድሏል ከአገር እንዲሰደዱም አድርጓል። ለምሳሌ በ2003 ዓም የኢትዮጵያ ፓርላማ ከቤተመንግሰት የተላለፈለትን ትዕዛዝ አክብሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ነፃነት መከበር የሚታገለዉን የግንቦት 7 ንቅናቄ ሽብርተኛ አድርጎ ፈርጇል። ይህ ፈር የለቀቀ ፍረጃ ደግሞ ወያኔ የሱን ዘረኛ ስርዐት የሚቃወሙ ግለሰቦችን፤ ሀሳባቸዉን በነፃነት የሚገልጹ ዜጎችን፤ ጋዜጠኞችን፤ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና ከወያኔ ጋር አናብርም ያሉ ወጣት ኢትዮጵያዉያንን “ግንቦት ሰባቶች” ናችሁ እያለ በጅምላ እያሰረ እንዲያሰቃይ ህጋዊ ሽፋን ሰጥቶታል። ለምሳሌ ከፍትህና ከነጻነት ጥማት ዉጭ ከግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ምንም አይነት ግኑኝነት የሌለዉን የፖለቲካ ፓርቲ መሪዉን አንዱአለም አራጌን፤ ታዋቂዉን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና መምህርት ርኢዮት አለሙን የግንቦት 7 አባላት ናቸዉ የሚል ሰንካላና መሠረተ ቢስ ክስ መስርቶ ለረጂም ዘመን እስራት ዳርጓቸዋል።
ወያኔ እንደ ዛሬዉ ከተማ ዉስጥ ሆኖ ሥልጣን ሳይቆጣጠር ገና ጫካ ዉስጥ እያለ ጥርሱን ከነከሰባቸዉና ከተቻለ አጠፋቸዋለሁ ካለዚያም አሽመደምዳቸዋለሁ ብሎ አስራ ሰባት አመት ሙሉ ከተዘጋጀላቸዉ የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የአማራ ብሄረሰብ ነዉ። በለስ ቀንቶት ሥልጣን ከጨበጠ ማግስት ጀምሮም በወሎና በጎንደር በኩል ከትግራይ ጋር የሚያዋሰኑ ሰፊ የሆነ ለም መሬቱን ጠቅልሎ በመውሰድ ዘረኛ ሥርዓቱን ዕድሜ ሊያራዝሙልኛል ይችላሉ ብሎ የሚተማመንባቸውን የቀድሞ የትግል አጋሮቹንና ካድሬዎቹን አስፍሮበታል:: ይህ በደልና ግፍ አልበቃ ብሎትም ቀደምቶቹ የኢትዮጵያ ገዥዎች ለፈጸሙት ግፍና የአስተዳደር በደሎች ሁሉ አማራዉን በጅምላ ተጠያቂ የሚያደርግ ፕሮፖጋንዳ እነሆ እስከዛሬ በመርጨት ለዘመናት በሠላም ከኖረው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር በጠላትነት እንዲተያይ አድርጎታል:: በወያኔ አጋፋሪነት በበደኖ ፡በአርሲ በአረካና ሌሎች አካባቢዎች አማራው ላይ በግፍ የተፈጸመው ጭፍጨፋና ከ2004 እስከ 2005 ዓም አማራዉን ከጉራፈርዳና ከቤንሻንጉል ለማፈናቀል የተወሰደው እርምጃ የዚህ የወያኔ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ውጤት መሆኑን የሚስት የለም::

አባ መላም፣ አባ ዱላም ሆነው ብቻ ኢሃዴግዬ በተሻላት


abamela-11


ኢሃአዴግዬን እንደኛ የሚወዳት ማን አለ… እውነቴን ነው የምላችሁ በፖሊሲዋ ተምረን በፖሊሷ ተገርፈን አድገን ዛሬ አንወድሽም ልንላት እንዴት ይቻለናል… ኢሃአዴግን ስለምንወዳት ነው በታመመች ጊዜ ትታከም፣ በሰከረች ጊዜ አልኮል ትቀንስ እያልን የምንወተውተው።
እንጂማ እብደቷ ካገር አባሮ እስኪያጠፋት ስካሯም አዙሮ እስኪደፋት ዝም ብለን እንጠብቅ አልነበርምን…
ኢሃአዴግዬ ታማለች! የሚለው ምንም ጥያቄ የለውም አከራካሪው ህመሙ መቼ ነው የጀመራት የሚለው ነው። አንዳንድ ወገኖች “ግንቦት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት ዓመተ ምህረት” ያለች እለት የጀመራት ነው ሲሉ፤ ሌሎች ደገሞ “የለም ገና ከእናቷ (ወይዘሮ ጫካ) ማህፀን እንዳለች ነው
የተለከፈችው” ይሉናል። ሌሎችም “ኧረ እሰከ ቅርብ ጊዜ ሰላም ነበረች አሁን እኮ ነው እያየናት እየለቀቀች እየለቀቀች የመጣችው” ይሏታል… አሁንም ሌሎች ያኔ አቶ መለስ ያገኙላት “የመበስበስ አደጋ” የተባለው በሽታ ነው ራሷ ላይ ወጥቶ የሚጫወትባት እያሉ መላ ምት ያቀረባሉ።
የሆነው ሆኖ ግን ኢሃአዴግ ታማለች! ይሄ እንኳን ሌላ “ዶክተር” መለስም የረጋገጡት ጉዳይ ነው። በህመሟ ሳቢያ ነው ያገኘችውን ሁሉ ልቀፍ፣ ትኩር ብሎ ያየኝን ሁሉ ወይ ልግርፍ ወይ ልሰር የሚያስብላት… ባጠቃላይ ሀመሟ መላ ቅጥም የለው።
የሚያሳዝነው ታድያ መታመሟ አይደለም ህምምማ የማንም ነው። ቸግሩ፤ የደረሰባቸው ሰዎች፤ “ህመምተኛ ሲብስበት አስታማሚ ይውፍራል” ብለው እንደሚተርቱት ኢሃአዴግዬ (እናቴ፣ አናቴ፣ ግንባሬ… ብዬ ስቀስቅ ብዬ ላልቅስ እንዴ…) ኢሃአዴግዬ በብርቱ ታማ ሳለ አስታማሚዎቿ እና አሳማሚዎቿ እየወፈሩ እየወፈሩ የመጡበት ሁኔታ ነው ያለው።

Tuesday, March 11, 2014

ሞት የስብሐት ነጋ በርን እያንኳኳ ነው (ሁኔ አቢሲኒያዊ ከፒተርቦሮው ዩ.ኬ)


አቶ ስብሃትን ጠጋ ብለው የሚያውቁት ሰዎች “አቦይ ብላችሁ አትጥሩት። አባታዊ አንደበትና ምግባር የለውም እርሱን አቦይ ማለት ትግራይ የሽማግሌ መሀን እንደሆነች መቁጠር ነው” ይሉታል፡፡
ሰውዬው ስብሐት ነጋ የህወሓትን አመሰራረት ቅድመ ታሪክ ለሚያውቅ ሰው ምን ያህል ተንኮለኛ እና በዘር ልክፍት የተለከፈ እንደሆነ ግልጽ ይሆንለታል፡፡ በ1963 ዓ.ም እንደተመሰረተ የሚነገርለት ማገብት (ማህበር ገስገስቲ ብሔረ ትግራይ) የተመሰረተው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትግራይ ተወላጅ ተማሪዎች ነበር፡፡ የማህበሩ ተልእኮም የተለያዩ የበጐ አድራጐት ስራዎችን በክረምት ወደ ትግራይ በመሄድ ማከናወን የሚል ነበር፡፡ በሂደት ሙሉ በሙሉ ወደ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በመቀየር ለተሐህት/ህወሓት መመስረት መሰረት ሆነ ለዚህ ዓላማ የማስቀየር ስራ ትልቁን አስተዋፅኦ ካደረጉት መካከል ደግሞ ዛሬ ታሞ የሚማቅቀው ስብሐት ነጋ አንዱ ነው፡፡Sebhat Nega TPLF king maker
ስብሐት ነጋ የህወሀትን መስመር እና ዓላማ መሀንዲስ ከመሆንም አልፎ እስከዛሬ ለብዙ ሰዎች ምስጢር በሆነ መልኩ መለስ ዜናዊንም ወደ ህወሀት ሊቀመንበርነት ብሎም የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስተር ያደረገ እና በህወሀት ክፍፍል ወቅትም ትልቅ ሚና ከነበራቸው ቀደምት የህወሀት ታጋዮች አንዱ ነው፡፡
ለባለፉት 23 ዓመታት የኢትዮጵያን ህዝብ ከጀርባ ሆነው ሲያንቀጠቅጥ የነበረው አይተ ስብሐት ነጋ እርሱም ተራው ደርሶ ቤልጅየም ብራሰልስ በሚገኘው ሴንት ሚካኤል ሆስፒታል Hôpital Saint Michel – (Brussels) መመላስ ከጀመረ 11 ዓመታት እንደሞላው የውስጥ አዋቂዎች ቢገልፁም የበሽታው አይነትና የሰውዬው የጤንነት ሁኔታ እስካሁን ድረስ ከቅርብ ሰዎች ውጪ ሳይወጣ ቀርቷል ሆኖም የህወሀት የውስጥ ሹኩቻን ተከትሎ ሚስጥሮ እያፈተለኩ መውጣታቸውን ቀጥለው ዛሬ ስለ ስብሀት ነጋ ጤንነት በተመለከተ ለዚህ ጽሁፍ ፀሀፊ አፈትላኪ መልዕክት ደርሷል፡፡

Monday, March 10, 2014

ዛሬ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የሰማያዊ ፓርቲ ሁለት ከፍተኛ አመራሮችና አባሎች ለመጋቢት 5 ተቀጠሩ


ዛሬ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የሰማያዊ ፓርቲ ሁለት ከፍተኛ
እሁድ ለት በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ሩጫ ላይ ለነፃነት እንሩጥ በሚል መርህ በሩጫው ላይ በመሳተፍ በርካታ ፖለቲካዊና መሀበራዊ ጥያቄዎችን ያነሱ የሰማያዊ ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊዎችና አባላት እንዲሁም ሰፍራው ንበረቶ ነን ቻቸውን ይዘው የነበሩ ሁለት የፓረቲው ከፍተኛ አመራሮች እና አንድ አባል ታፍሰው ወደ ሾላ የካ ፖሊሰ መምሪያ መወሰዳቸው ይታወቃል ፡፡
በዛሬው እለትም ፍርድቤት ቀርበው የተከሰሱበትን ምክንያት መርማሪ ፖሊሱ /ኮማንደር የማታ/አብራርቷል፡፡ የተከሰሱበት ምክንያት እሁድ በተካሄደው የሴቶች ሩጫ ላይ ተመሳስሎ በመግባት የጣይቱ ልጆች ነን ፣ የምኒልክ ልጆች ነን ፣ ኑሮ መረረን ፣ የህሊና እስረኞች ይፈቱ በሚል ሁከትን ለማነሳሳት ቀስቅሳችኋል የሚልኘ ሲሆን መርማሪው መረጃ አሰባስቤ ስላልጨረስኩና መረጃዎቼን ያጠፋሉ ሰዎችንም እንዳይመሰክሩ ያስፈራሩብኛል በተጨማሪም ብዙዎቹ ቋሚ አድራሻ የሌላቸው ስለሆነ መረጃ እስካሰባስብ የ15 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ ብሏል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮችም እድል እየጠየቁ ለማስረዳት ጥረት ያደረጉ ሲሆን የተከሰሱበት ምክንያት ሀሳባቸውን በአጋጣሚው በነፃነት በመግለፃቸውና በተባለው መልኩ ሳይሆን አስበው እና ሩጫውንም እንደማንኛውም ሴት ኢትዮጵያዊ ቲሸርት ገዝተውና ተመዝግበው ሲሆን አሉ የተባለውን እንዳሉ አስረግጠው ነገር ግን ሁከት አለማስነሳታቸውንም እንዲሁም ሩጫው ሲጠናቀቅ አፍሰው እስርቤት እንደወሰዷቸው ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ አብረው የታሰሩት ወንዶችም በወቅቱ በቦታው የጓደኞቻቸውን እቃዎች ተሸክመው ሩጫውን እስኪፈፅሙ እየጠበቁ በነበረበት ሰዓት ሴቶቹን እየለቀሙ ሲወስዱ ለምንድነው የምትወስዷቸው በማለታቸው ብቻ አብረው እንደታሰሩ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ አክለውም እኛ ህጋዊ ሰውነት ያለን የፓርቲ አመራሮችና አባላት ነን ስራችንም በዚሁ በአዲስ አበባ ሆኖ ሳለና በተፈለግን ጊዜ የምንገኝበት ግልፅ አድራሻ በምርመራ ወቅት ተመዝግቦ እያለ ዋስትና አይሰጣቸው የተባለው ተቀባይነት የለውም እንዲሁም መረጃ ላሰባስብ የሚለውም ምክንያት ሁሉም ንብረቶቻችን በወቅቱ ተወስደው በፖሊሶች እጅ የሚገኝ ስለሆነ ተገቢ አይደለም በሚል ፍርድ ቤቱን ሞግተዋል፡፡

የኢሕአዴግ አባል ፓርቲዎች በዶ/ር ደብረጽዮን ፍቃድ ካልሆነ ምንም ዓይነት ውሳኔ መስጠት እንደማይችሉ ተገለጸ


የደህንነት ሹሙ አቶ ጌታቸው አሰፋና ባለስልጣኖቻቸው በሙስና እና በዘረፋ ላይ ተሰማርተዋል
የፍርድ ቤቶች እና የተቃዋሚ ፓርቲዎችን እንቅስቃሴ ማኮላሸት ለአለቃ ጸጋዬ በርሄ ተሰቷቸዋል
የጦር ሰራዊቱን በተጠንቀቅ የሚከታተሉ ወታደራዊ ደህንነቶች ተደራጅተው በየእዙ ተበትነዋል
ምኒልክ ሳልሳዊ
በመከላከያ ሰራዊት የሕወሓት መኮንኖች ስር የሰደደው የሙስና እና የዘረፋ አድራጎት በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥም ከሹሙ ከአቶ ጌታቸው እና ከባለስልጣኖቻቸው ጀምሮ እስከ ገራፊዎች ድረስ መንሰራፋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል:: እንደውስጥ አዋቂ ምንጮቹ መረጃ ከሆነ የደህንነት ባለስልጣኖቹ የተዘፈቁበት የሙስና ተግባር በተጨማሪ ዘረፋን እና ሴት መድፈርን እንዲሁም የቡድን ወንጀሎችን ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል::በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ባለሃብቶችን በማስፈራራት ከፍርድ ቤት ትእዛዝ ውጪ በማሰር እንዲሁም የሙስና ወንጀል ተገኝቶብሃል ይህን ያህል ገንዘብ አምጣ ካላመጣህ እንገድልሃለን እስከማለት በከመድረሳቸውም በተጨማሪ ይህንን ጉዳይ ለፖሊስ የጠቆመ ባለሃብት በማፈን ንብረቱ ባማገድ እና በተለያዩ ስልቶች የተጠየቀውን ገንዘብ እንዲሰጥ በማስገደድ ላይ መሆናቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል::
ከዚህ ቀደም በሙስና የተከሰሱ የስርኣቱ ባለስልጣናትን ተገን በማደርግ በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ባለሃብቶችን በመከታተል እና ደህንነት ቢሮ ድረስ በመውሰድ በሙስና ከታሰረው ስም እየተጠቀሰ … ከሚባል ባለስልጣን ጋር ግንኙነት አለህ ማስረጃ ተገኝቶብሃል በማለት በፈጠራ ወንጀል ባለሃብቱን በመዝረፍ ስራ ላይ ተሰማርተው የነበረ እና እንዲሁም የአዲስ አበባን ቆነጃጅት ቢሯቸው ድረስ በግብረአበሮቻቸው አፋኝነት እና አስገዳጅነት በመውሰድ ካለፍላጎታቸው አስገድደው በመድፈር ላይ ናቸው ያሉት ምንጮቹ ተራ የደህንነት አባላት ለዚሁ ተልእኮ ተሰማርተው የሚሰሩት ምንም አይነት ወንጀል በቡድን ሲፈጽሙ የሚጠይቃቸው አለመኖሩን የሕዝቡን በደል የከፋ አድርጎታል::
ኢትዮጵያውያን በሕወሓቱ የደህንነት መዋቅር የሚመራ የሽብር ተግባራትን አጥብቆ ስለሚፈራ እና በየጊዜው በሕወሓት ደህንነቶች መሪነት የሚወሰዱ እርምጃዎች በሃገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ስጋትን በመፍጠራቸው በየእስር ቤቱ የሚካሄዱ ሕገወጥ ጸረ ፍትህ ተግባራት እና የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የኢትዮጵያውያን የቀን ተቀን አጀንዳ ሆነው መምጣታቸው ገዢው ፓርቲ ሕዝቡን ምን ያህል እንዳሸበረ ይጠቁማል ሲሉ ምንጮሹ አክለው ገልጸዋል::

Sunday, March 9, 2014

Women from Semyawi party and supporters of Semayawi party’s cause protested during “Ladies great run” in Addis Ababa. Ethiopians applauded the courageous women on social Medias by saying “Proud of you our Sisters!”
ሰበር ዜና (BlueParty Ethiopia)

ዜና በጨዋታ፤ ወደፊት የሚወጣውን አዋጅ የጣሱ ሴቶች ታሰሩ

1904253_693601320682469_528107450_n

ወደፊት የሚወጣውን አዋጅ የጣሱ ሴቶች ታሰሩ፤
ለአለም አቀፉ የሴቶች ቀን ክብረ በአል በተዘጋጀ የሩጫ ዝግጅት፤ በሀገራችን ሰላም አጣን ሲሉ ሃሳባቸውን የገለጹ ሴቶች በቁጥጥር ስር ዋሉ፤
ከስፍራው የደረሰን ዜና እንደሚያስረዳው ሴቶቹ እንደተለመደው ባሎቻቸውን እየኮነኑ መንግስትን ማሞካሽት ሲገባቸው እነርሱ ግን መንግስትን በመኮንን በሀገራችን ሰላም አጣን በማለት ድምጻቸውን ከፍ አድርገው አሰምተዋል። ከዛም አልፈው ተርፈው ቀኑ ደረስ ቀኑ ደረሰ… እያሉ የምርጫ ቀን መቃረቡን በመጠቆም ኢሀአዴግ ላይ ፍርሃት ለቀውባታል።
ሴት እህቶቻችንን ሃሳባቸውን ከመግለጽ ወጪ የሰሩት ጥፋት ምን ሆኖ ነው የታሰሩት ብለን ያልጠይቅናቸው የመንግስት ተበካይ፤ ሃሳብን በአደባባይ መግለጽ ምንም እንኳ ለጊዜው በሽብርተኝነት አዋጁ ላይ ባይጠቀስም በመንግስታችን እና በድርጅታችን ላይ ታላቅ ሽብር እየፈጠረ በመሆኑ ወደፊት እናካትተዋለን የሚለውን ታሳቢ በማድረግ ሴቶቹ ወደፊት የሚወጣውን አዋጅ በመጣሳቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል ሲሉ ግራ አጋብተውናል።
የሴቶቻችንን ድምጽ ከሰማያዊ ፓርቲ ፌስ ቡክ ላይ አገኝተን ድረ ገጻችን ላይ አድርገነዋል፤

Friday, March 7, 2014

ሰላማዊ ወይስ የትጥቅ ትግል ወይስ ማንፈራጠጥ


gun

የተማረ ወይም የእውቀት ባለቤት እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ክፍል ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል ሰላማዊ ይሁን ወይስ በትጥቅ ትግል የሚለውን የጦፈ ክርክር ሲያደርግ ሃያ ሁለት ዓመታት ሆነው፤ ዳኛ የሌለበት ክርክር ስለሆነ የመደማመጥ ግዴታ ታይቶበት አይታወቅም፤ ስለዚህም በሁለቱ መሀከል ያለው ልዩነት ግልጽ ሆኖ አያውቅም፤
አንድ፣ ከሁሉ በፊት ሰላማዊ ትግል በሀሳብ ደረጃ መሆኑንና የትጥቅ ትግል ደግሞ በተግባር መሆኑን ለይቶ ለመረዳት ችግር ሆኖ ቆይቶኣል፤ በሌላ አነጋገር ሰላማዊ ትግል በሀሳብ፣ በንግግር፣ በተለያዩ ሀሳብን ለማስለወጥ መቀስቀሻ በሚሆኑ መንገዶች ተቃውሞን መግለጽ ነው፤ በአንጻሩ የትጥቅ ትግል በጠመንጃ ወይም በጉልበት ያለውን የአገዛዝ ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረግ ሙከራ ነው፤
ሁለት፣ እንዲህ ከሆነ በሰላማዊ ትግል ለሚያምኑ ሰዎች ያለምንም ጥርጥር በተለያዩ ዓላማዎችና ዘዴዎች ላይ መከራከርና ሀሳብን ማጥራት አስፈላጊ ነው፤ በሰላማዊ ትግል ተግባር አለ ቢባልም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የድጋፍ ወይም የተቃውሞ አቅዋሞችን ከማሳየት አያልፍም፤ አገዛዞች ጃዝ! ብለው ውሻና ፖሊስ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ሲለቁ የጉልበት ጥርስና ዱላ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያርፋል፤ ጉዳት ይደርሳል፤ ሰላም ይቃወሳል፤ በሕዝብና በአገዛዙ መሀከል ቂም ይጀመራል።
ሦስት፣ የትጥቅ ትግል ደግሞ በተዋረድ በሚተላለፍ ትእዛዝ የሚፈጸም ግዴታ ነው፤ በትጥቅ ትግል ጉልበተኛ ከጉልበተኛ ጋር፣ ብረት ከብረት ጋር ይጋጠማል፤ የሰው ልጅ ለእርድ ይቀርባል፤ በሕይወታቸው በልተው ያልጠገቡ ምስኪኖች ለጥቂት ሰዎች የሥልጣን ጉጉት ይታረዳሉ፤ ያለቀባሪ በጅብና በአሞራ ይበላሉ፤ ዕድለኞች የሚባሉት እጆቻቸው፣ ወይም እግሮቻቸው ተቆርጠው፣ ወይም ዓይኖቻቸው ጠፍተው፣ ወይም ከዚህ ሁሉ የባሰ ጉዳት ደርሶባቸው በሕይወት የሚቀሩት ናቸው፤ ከነዚህ በሕይወት በቀሩት የጦር ጉዳተኞችና በጦርነቱ ላይ በሞቱት መሀከል የትኛው የተሻለ አንደሆነ የሞቱት ባይናገሩም ጉዳተኞቹ ይናገራሉ፤ ‹የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ!› እያሉ።
አራት፣ ሁለቱ የትግል ስልት ዓይነቶች በባሕርይ የተለዩ ናቸው፤ አንዱ ሌላውን የሚደግፍ አይደለም፤ ሰላማዊ ትግል የትጥቅ ትግልን ለመደገፍ ሰላማዊ የሚለውን ስያሜ መጣል አለበት፤ የትጥቅ ትግልም ሰላማዊ ትግልን ለመደገፍ ትጥቅ የሚለውን ስያሜ መተው አለበት፤ ሰላማዊ ትግልና የትጥቅ ትግል አራማጆች ድል ቢያደርጉ ማን ወንበሩ ላይ እንደሚወጣ ሳይታለም የተፈታ ነው፤ ጠመንጃ የያዘው ሥልጣኑን ሲይዝ ሰላማዊ ትግሉ ይቀጥላል! ያውም ከተፈቀደለት!

ወያኔ በግንቦት 7 ስም ሠላማዊ ዜጎችን ማሰቃየቱን ባስቸኳይ ማቆም አለበት

ባለፉት አራትና አምስት አመታት በግልጽ እንዳየነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እኩልነቱን፤ መብቱንና ነጻነቱን ለማስከበር የሚያደርገዉ ትግል ጫና በፈጠረበት ቁጥር ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የራሱን ህገመንግስት የሚደፈጥጡ ህጎች አርቅቆ አያጸደቀ ሠላማዊ ዜጎችን አስሯል፤ ገድሏል ከአገር እንዲሰደዱም አድርጓል። ለምሳሌ በ2003 ዓም የኢትዮጵያ ፓርላማ ከቤተመንግሰት የተላለፈለትን ትዕዛዝ አክብሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ነፃነት መከበር የሚታገለዉን የግንቦት 7 ንቅናቄ ሽብርተኛ አድርጎ ፈርጇል። ይህ ፈር የለቀቀ ፍረጃ ደግሞ ወያኔ የሱን ዘረኛ ስርዐት የሚቃወሙ ግለሰቦችን፤ ሀሳባቸዉን በነፃነት የሚገልጹ ዜጎችን፤ ጋዜጠኞችን፤ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና ከወያኔ ጋር አናብርም ያሉ ወጣት ኢትዮጵያዉያንን “ግንቦት ሰባቶች” ናችሁ እያለ በጅምላ እያሰረ እንዲያሰቃይ ህጋዊ ሽፋን ሰጥቶታል። ለምሳሌ ከፍትህና ከነጻነት ጥማት ዉጭ ከግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ምንም አይነት ግኑኝነት የሌለዉን የፖለቲካ ፓርቲ መሪዉን አንዱአለም አራጌን፤ ታዋቂዉን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና መምህርት ርኢዮት አለሙን የግንቦት 7 አባላት ናቸዉ የሚል ሰንካላና መሠረተ ቢስ ክስ መስርቶ ለረጂም ዘመን እስራት ዳርጓቸዋል።

ወያኔ እንደ ዛሬዉ ከተማ ዉስጥ ሆኖ ሥልጣን ሳይቆጣጠር ገና ጫካ ዉስጥ እያለ ጥርሱን ከነከሰባቸዉና ከተቻለ አጠፋቸዋለሁ ካለዚያም አሽመደምዳቸዋለሁ ብሎ አስራ ሰባት አመት ሙሉ ከተዘጋጀላቸዉ የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የአማራ ብሄረሰብ ነዉ። በለስ ቀንቶት ሥልጣን ከጨበጠ ማግስት ጀምሮም በወሎና በጎንደር በኩል ከትግራይ ጋር የሚያዋሰኑ ሰፊ የሆነ ለም መሬቱን ጠቅልሎ በመውሰድ ዘረኛ ሥርዓቱን ዕድሜ ሊያራዝሙልኛል ይችላሉ ብሎ የሚተማመንባቸውን የቀድሞ የትግል አጋሮቹንና ካድሬዎቹን አስፍሮበታል:: ይህ በደልና ግፍ አልበቃ ብሎትም ቀደምቶቹ የኢትዮጵያ ገዥዎች ለፈጸሙት ግፍና የአስተዳደር በደሎች ሁሉ አማራዉን በጅምላ ተጠያቂ የሚያደርግ ፕሮፖጋንዳ እነሆ እስከዛሬ በመርጨት ለዘመናት በሠላም ከኖረው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር በጠላትነት እንዲተያይ አድርጎታል:: በወያኔ አጋፋሪነት በበደኖ ፡በአርሲ በአረካና ሌሎች አካባቢዎች አማራው ላይ በግፍ የተፈጸመው ጭፍጨፋና ከ2004 እስከ 2005 ዓም አማራዉን ከጉራፈርዳና ከቤንሻንጉል ለማፈናቀል የተወሰደው እርምጃ የዚህ የወያኔ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ውጤት መሆኑን የምስት የለም::
ሟቹ መለስ ዜናዊና በህይወት የሚገኙ ቀንደኛ የወያኔ መሪዎች የተጠናወታቸው የአማራ ጥላቻ በጸረ ፋሽስት ዘመቻ ወቅት ባንዳ ከነበሩ አባቶቻቸዉና አያቶቻቸዉ የተወረሰ ፋሽስት ጣሊያን ለደረሰባት ሽንፈት በዘርና በሃይማኖት ተከፋፍለን እርስ በርሳችን እንድንጠፋፋ ተክላብን የሄደቺው ተንኮል አካል ነው ::