Saturday, July 20, 2013

ነፃነት የማያውቅ ነፃ አውጭ፦ ህወሀት

ነፃነት የማያውቅ ነፃ አውጭ፦ ህወሀት

የህወሀት መስራቾች “መግለጫ” በሚል ርዕስ በ1968 ካሰራጩት በባለ 28 ገፁ በእጅ የተፃፈው ማኒፌስቷቸው መቅድም ላይ እንዲህ ይላል “ይህ መፅሔት የትግራይ ሕዝብ ሀቀኛ ወኪል የሆነው የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ ድርጅት (ተ.ኀ.ህ.ት)መግለጫና የትግሉ መመሪያ ነው።ልብ በሉ ህወሀት ገና በምስረታው ትግል ሳይጀምርና በትግራይ ሕዝብ ሳይወከል ራሱን ግን የምስኪኑና ጭቁኑ ሕዝብ ወኪል አድርጎ እንዲያውም ከወኪሎች ሁሉ አልቆ “ሀቀኛ ወኪልነትን” ለራሱ ሸልሟል።ህወሀት ከ1968 ዓ.ም በኋላ ለትግራይ ሕዝብ የምታገለው እኔ ብቻ ነኝ ከኛ ከህወሀቶች ውጭ በትግራይ ውስጥ ማንንም ማየት አልፈልግም አለ።ይህንንም አስታኮ ተነሳሁበት ያለውን አላማ ወደጎን አድርጎ ትግራይ ውስጥ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ድርጅቶች ላይ ዘመቻ ጀመረ የመጀመሪያው ሰለባ በዮሀንስ ተክለሀይማኖት የሚመራው እንደ ህወሀት ትግራይን ለመገንጠል የሚታገለው የትግራይ ነፃነት ግንባር ሆነ ህወሀት በዚህ አላበቃም በራስ መንገሻ የሚመራው ኢዲዩም ከደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ ከትግራይ እንዲሸሽ ተደረገ።ከሁሉ የባሰውን ወንጀል ህወሀት የሰራው ግን የኢህአፓ አባል በሆኑ የትግራይ ተወላጆችና በኢህአፓ የጦር ክንፍ ኢህአሰ ላይ ነበር።በመጀመሪያ ኢህአሰ ከትግራይ የጦር ሰፈሩ ከአሲንባ ለቆ እንዲወጣ የፈለጉት የህወሀት አመራሮች ትግራይ ውስጥ በኢህአፓ ስር በትግራይ ተወላጅ አባሎቹ የተዘረጋውን መዋቅር ለደርግ አሳልፋ በመስጠት እንዲሁም ደርግን ሰርጎ በመግባት የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የኢህአፓ አባሎች ብቻ ሳይሆኑ ከህወሀት ጋር አልቆም ያሉ በርካታ የትግራይ ተወላጆች የቀይሽብር ሰለባ እንዲሆኑ አድርገዋል።የኢህአፓ የጦር ክንፍ የሆነውን ኢህአሰን ደግሞ ሰርጎ በመግባት እና እንቅስቃሴውን ለደርግ አሳልፎ በመስጠት እንዲሁም በተደጋጋሚ ጊዜ ጦርነት በመግጠም ከሁለት ሀይል ጋር ከደርግም ከህወሀትም ጋር ጦርነት የገባው የኢህአሰ ጦር ከፓርቲውና ከጦሩ አማራር ችግር ጋር ተዳምሮ ኢህአሰ ትግራይን ለቆ እንዲወጣ ሆኗል።
የጫካ ባህሪው ያልለቀቀው ህወሀት አራት ኪሎ ቤተመንግስት ሲከትም ከነጫካ ባህሪው ነበር አይደለም በትግራይ በመላው ኢትዮጵያ ከኔ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ አልይ አለ ይኸው ባህሪው ለ22 ዓመታት በኢትዮጵያችን ተንሰራፍቶ የኋላ ታሪክ እየጠቀሰ ቁልፍ የመንግስት ስልጣኖችን ፣ ፖሊስ መከላከያ ሰራዊትንና ደህንነትን ፣ የሀገሪቱን ኢኮነሚ ፣ ሚዲያውን ምን የቀረ አለ ከስትንፋሳችን ውጭ ያለውን ነገር በሙሉ ተቆጣጥሮ የሰቆቃ ህይወትን እንድንገፋ ተገደናል በሁኑ ከእንግዲህ ዘርና ብሔርን መሰረት ባደረጉ ነፃነት የማያውቁ ነፃ አውጭዎች ስር ለመተዳደር መሻት ይኖርብናል!?

No comments:

Post a Comment