Sunday, July 14, 2013

የአፍሪቃ ኅብረት፣ መፈንቅለ መንግሥትና ፈታኙ አቋም

አንድ ቢሊዮን ገደማ ህዝብ ባለው ክፍለ ዓለም 54 አባል ሃገራትን ያቀፈውና ዘንድሮ 50 ኛ ዓመቱን በማክበር ላይ የሚገኘው የአፍሪቃ ኅብረት በየጊዜው በሚከሠቱ የአህጉሩ ችግሮች መፈተኑ አልቀረም ። የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ወይዘሮ እንኮሳዛና ድላማኒ
ዙማ ፣ በቅርቡ በግብጹ ፕሬዝዳንት መሐመድ ሙርሲ ከሥልጣን ገለል እንዲሉ የተደረገበትን እርምጃ መነሻ በማድረግ ፤ኅብረቱ ከግብፅ ህዝብ ጎን እንደሚቆም ፤ሆኖም አገሪቱ ለጊዜው ከአባልነት እንደምትታገድ መጠቆማቸው የሚታወስ ነው ። ይህ ጊዜያዊ ወይስ ዘለቄታ ያለው የኅብረቱ መርኅ ነው? «የአፍሪቃ ኅብረት፣ መፈንቅለ መንግሥትና ፈታኙ አቋም ፣»የዛሬው የእንወያይ ዝግጅት ትኩረት ነው በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር 3 እንግዶችን ጋብዘናል ። እነርሱም
1.የፖለቲካ ሳይንስ ፕሮፌሰር፣እንዲሁም የኦሮሞ ፌደራል ኮንግረስ ሊቀመንበር ፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና
2.የፀጥታ ጥናት ተቋም ባልደረባ ዶክተር ሰሎሞን አየለ ደርሶ እንዲሁም
3. የቀድሞ የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ባልደረባና ጋዜጠኛ አቶ ንጉሤ ደስታ ናቸው

No comments:

Post a Comment