Saturday, March 15, 2014

የኢህአዴግ ማመልክቻ ድጋሚ ውድቅ መደረግ አለበት!


በመጀመሪያ አፋኝ ሕጎች መሠረዝ አለባቸው!
የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) ለተሰኘ ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ በድጋሚ ያቀረበው የእውቅና ጥያቄ ማመልከቻ ውድቅ መደረግ እንዳለበት ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት (Human Rights Watch) ድርጅት አስታወቀ፡፡ ኢህአዴግ የእውቅና ማመልከቻ አስገብቶ ውድቅ ተደርጎበት የነበረ ሲሆን በኢትዮጵያ ላይ የታወጁት አፋኝ ሕጎች እስካልተወገዱ ድረስ ድጋሚ ማመልከቻው ውድቅ ሊደረግ እንደሚገባው ጨምሮ ተነግሯል፡፡
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከሳምንታት በፊት “
ክሌር ሾርት
ዛሬ የወጣው የሰብዓዊ መብት ድርጅት መግለጫ ይህንኑ የኢህአዴግን ጥያቄ የሚያስረዳ ሲሆን በአፋኝ ህጎቹ ላይ አንዳችም ለውጥ ያላሳየው ኢህአዴግ ማመልከቻው ውድቅ መደረግ እንዳለበት መግለጫው በአጽዕኖት ይናገራል፡፡ ምክንያቱንም ሲጠቅስ “የኢትዮጵያ መንግሥት ሚዲያውን አፍኗል፤ (ሰብዓዊ መብት እንዲከበር) እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሁሉ አድቅቋል” በማለት ያስረዳል፡፡ ኢህአዴግ ከዚህ በፊት ባስገባው ማመልከቻ ላይ የEITI ቦርድ ውሳኔውን ሲያስተላልፍ “የመያዶች ሕግ የተሰኘው አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆን እስካልተደረገ” ማመልከቻው ሊታይ እንደማይገባው በዋንኛነት ማመልከቻው ውድቅ እንዲደረግ የተደረገበት ምክንያት እንደነበር የጠቀሰው የሰብዓዊ መብት ድርጅት መግለጫ EITI አሁንም ይህንኑ ውሳኔውን እንዲያከብር ጠይቋል፡፡
ማመልከቻው እንደገና እንዲታይና የቦርዱ የቀድሞ ውሳኔ እንዲቀለበስ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የቀድሞ የእንግሊዝ ዓለምአቀፍ ትብብር ሚ/ር የሆኑት ክሌር ሾርት መሆናቸውን መግለጫው ያስረዳል፡፡ እኚህ ግለሰብ የአፍሪካ አምባገነኖችን በመደገፍ የሚታወቁ ሲሆን ይህ ከጥቅማቸው ጋር የተሳሰረው ግንኙነታቸው አሁንም ኢህአዴግን እንዲደግፉ እንዳደረጋቸው ይነገራል፡፡ እንዲሁም በሌሎች ኢህአዴግ ባቋቋማቸው ዓለምአቀፋዊነት ሽፋን በተላበሱ ድርጅቶች ውስጥ የአመራር አባል በመሆን ሚስ ሾርት እንደሚያገለግሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የእንግሊዝ ፓርላማ አባል በነበሩበት ወቅትም ያላወጡትን ወጪ አውጥቻለሁ በማለት በብዙ ሺዎች የሚገመት ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ መሆናቸው በወቅቱ ዴይሊ ቴሌግራፍ ባወጣው መረጃ አጋልጦ ነበር፡፡ የተወሰነውን ገንዘብ የመለሱ ቢሆንም ጋዜጣው በወቅቱ ያወጣው መረጃ ግለሰቧ የሕዝብን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው የተጠቀሙ “ሙሰኛ” መሆናቸውን ያስረዳል፡፡
ከእነዚህና ሌሎች መረጃዎች አኳያ ኢህአዴግ በየቦታው እየደለለ “ባስቀመጣቸው” በመጠቀም የፈለገውን ለማድረግ ሲሞክር ዝም ሊባል እንደማይገባው በዚሁ ጉዳይ ላይ በከፍተኛ ሁኔታ የሚንቀሳቀሰውን የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄን ጠቅሶ ጎልጉል መዘገቡ ይታወሳል፡፡
የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ መሠረት ኢህአዴግ የEITI አባል መሆን ከፈለገ ያወጣቸውን አፋኝ ሕጎች በሙሉ መሠረዝ እንዳለበትና የመናገር መብትን፣ የፕሬስ ነጻነትን፣ የመሰብሰብ፣ ወዘተ መብቶችን በይፋ ማክበር እንዳለበት እና የEITI የአባልነት ቅድመ መስፈርቶችንም በሙሉ ማሟላት እንደሚገባው ጨምሮ ገልጾዋል፡፡

No comments:

Post a Comment